Friday, 29 May 2020

ለኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን “መከፋፈል” ጊዜው ነውን?

Please read in PDF

  ከወደ ጐጃም የተሰማው ዜና መልካም አይመስልም፤ ቅብዐቶች ከኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አንድነት በመለየት የራሳቸውን አገረ ስብከት በመመስረት፣ ጳጳሳት መሾማቸው እየተሰማ ነው። ነገር ግን ይህ ምሳሌነቱ መልካም አይመስልም። በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ፕሮቴስታትንት ወይም ሐድሶአውያን ተብለው የማይወገዙ፣ ቢያንስ አራት ትምህርቶች አሉ፤ ቅብዐት፣ ጸጋ፣ ዘጠኝ መለኮትና ካራ፤ እኒህ ኹለቱ የትምህርት ይትበሃሎች ለዘመናት በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ [ከተወሰኑ ግጭቶች በቀር] በአብሮነት አሉ።

Wednesday, 27 May 2020

ዕርገቱ - የቤዝወታችን ፍጻሜና ተስፋችን!

Please read in PDF
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ማረጉ ባለፈው ሳምንት በምዕራባውያን አብያተ ክርስቲያናት፤ በዚህ ሳምንት ደግሞ በምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ዛሬ ይታሰባል፤ ዕርገቱን አንዱ ወንጌላዊ፣ በመንፈስ ቅዱስ መነዳት ኹለት ጊዜ ዘግቦልናል፤ ሉቃስ ወንጌላዊው፤ (ሉቃ. 2450-52 ሐዋ. 16: 11) ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱም ስለ ዕርገቱ አስቀድሞ ተናግሮአል፤ (ዮሐ. 142: 13 2017) ነቢያትም ትንቢት ተናግረውለታል፤ (ዳን. 79-13)

Sunday, 24 May 2020

“እመቤቴ ቤዛ ብትኾን ምንድር ነው?” (የማያልቀው የዶ/ር ዘበነ ለማ ተረት)

Please read in PDF

   ዶ/ር ዘበነ ለማ፣ በአገረ አሜሪካ የሬዲዮ ፕሮግራም አለው፤ ከጠያቂዎች ለሚመጣለት ጥያቄ ኹሉ መልስ የሚመልስበት። ትኩረቴን ከሳበውና ለዛሬ እንዳካፍላችሁ የፈለግኹት፣ በአንዲት እህት አማካይነት፣ በቤዛነት ዙሪያ የተጠየቀውንና የመለሰውን መልስ በማንሣት ይኾናል፤ የተዘጋጀው “የመናፍቃን ምላሽና የዶ/ር ቀሲስ መምህር ዘበነ ለማ መልስ ክፍል 6” በሚል ርእስ ነው። ለቀረበለት ጥያቄ ዘበነ የመለሰው፣ ጭምቀ ዐሳብ በአጭሩ እንዲህ የሚል ነው፦



Friday, 22 May 2020

ከ"ምኞት" ወይም ከ"ጉምዠታ" ወንጌል ተጠንቀቁ!


የብልጽግና ወንጌል መምህራን ብዙዎችን ካታለሉበት መንገድ አንዱ፣ ሥጋዊ አምሮትንና መሻትን ባልሞተው አዳም ውስጥ በማስገባት እና በመቀርቀር ነው። ይህ መንገድ ደግሞ ከዚህ ቀደም ሰይጣን ራሱ ያደረገውና ብክለትን ወደ ሰው ያስገባበት ጥበቡ ነው። በኢየሱስ ላይ ዓይኖቹ ትክ ያላሉ ኹሉ፣ በዚህ ጥበብ መታለሉ አይቀርም።

Thursday, 21 May 2020

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፭)

Please read in PDF


   ከዚህ ቀደም የስህተት መምህራን የማይነኳቸውን ሦስት ርዕሶችን ማለትም ኀጢአትን፣ ንስሐን፣ የእግዚአብሔርን ፍርድና ቊጣ መመልከታችን ይታወሳል፤ ዛሬ ደግሞ ቀጣዩን ርእስ እንመለከታለን።

4.
ስለ ቅድስና፦ ቅድስና በብሉይም ኾነ በአዲስ ኪዳን ውስጥ እጅግ የከበረ ዐሳብ ነው። በብሉይ ኪዳን በተለይም ከሕጉ መሰጠት በኋላ፣ ከቅድስና ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጠንካራው ቁልፍ ቃል፣ቅድስና ለእግዚአብሔርየሚለው ነው። ይህም በጥሩ ወርቅ በተሠራው አክሊል ላይ፣ እንደ ማኅተም ቅርጽ ተሠርቶ፣ ኹሉም ሰው ሊያየው በሚችል መልኩ፣ በራሱ ላይ አክሊሉን ይደፋዋል፤ (ዘጸ. 3930) በማኅተም ቅርጽ ያለውንቅድስና ለእግዚአብሔርየሚለውን ጽሕፈት ማንም ይሸሽገው ዘንድ አይችልም። ከእግዚአብሔር ጋር በመኾን፣ የተካፈልነውን ቅድስና እኛ ራሳችን እንኳ መሸሸግ አንችልም፤ ልክ ሙሴ የፊቱን ብርሃን መሸፈን እንዳልቻለው፤ (ዘጸ. 3429)

Sunday, 17 May 2020

የኅዳር በሽታ፤ ኮሮና፤ ዝሙት!

50 ሚሊየን በላይ ሕዝብ የቀጠፈው፣ ዓለም ዓቀፉ ብሪትሽ ፍሉ፣ በአገራችን ሲከሰት "የኅዳር በሽታ" መባሉንና የመጣበት ምክንያትም "ዘማዊ በምድሪቱ ስለ በዛ ነው" ተብሎ ይታመን እንደ ነበር ስንቶች ሰምተን ይኾን? [በእርግጥ በአገራችን አንድ ጥፋት ሲከሰት፣ ወዲያው ከመቅሰፍትና ከመዓት ጋር ማያያዙ የተለመደ ቢሆንም፣ በዚያ ዘመን ዝሙት የተስፋፋ መኾኑን በሚገባ ያሳብቃል] እግዚአብሔር ግን ምሕረቱ ብዙም፤ ለዘላለምም ነው!

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፬)

Please read in PDF

    3.  የእግዚአብሔርን ቊጣና ፍርድ አይናገሩም፦ ዓይን ያወጡ ሃሳውያን አገልጋዮች ብቻ ሳይኾኑ፣ በአከባቢያችን ያሉ አንዳንድ ለቀቅተኛ እንኳ፣ “የእግዚአብሔርን ፍቅር ብቻ ማውራት አይበቃምን?” ሲሉ፣ በተደጋጋሚ እንሰማቸዋለን። ነገር ግን ከተነገረውና በግልጥ ከተቀመጠው ከእግዚአብሔር ዐሳብ መራቅ አደጋ አለው፤ ደግሞም የመጽሐፍ ቅዱስን እውነተኛነትና አይሻሬነትን ማቃለል ነው።

Wednesday, 13 May 2020

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፫)

Please read in PDf

2.  ንስሐ፦ የስህተት መምህራን የማይነኩትና የማይደፍሩት ሌላው ርእስ ቢኖር ንስሐ ነው። ከእግዚአብሔር ለተለየው ዓለምም፤ በቤቱ ኖሮ ለሚበድለው አማኝም ንስሐ ዕለታዊ ተግባር ነው። በብሉይ ኪዳን ዐሳብ የአንድን ሰው ከኀጢአት ወደ እግዚአብሔር መመለስን የሚያመለክት ሲኾን (ኢሳ. 9፥13፤ ኤር. 4፥22፤ 5፥3፤ 26፥3፤ ሆሴ. 5፥4፤ 7፥10)፤ የአዲስ ኪዳን ምንባባት ደግሞ ኹለንተናዊ መመለስን የሚያመለክቱ ናቸው፤ ለምሳሌም፦ የነነዌ ሰዎች ኹለንተናዊ በኾነ ዝንባሌአቸው ንስሐ መግባታቸውን፣ “በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፥” በማለት ጌታ ኢየሱስ ተናገረ (ዮና. 3፥5-9፤ ማቴ. 12፥41)፣ ነነዌ ዮናስን ከተቀበለች፣ አይሁድም ከዮናስ የሚበልጠውን ጌታ አምነው ሊቀበሉ ይገባ ነበርና።

Saturday, 9 May 2020

Friday, 8 May 2020

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፪)

Please read in PDf

·        ኀጢአት፦ በስህተት መምህራን ዘንድ ትርጉማቸው ከተበላሹ ወይም እንደ ገና ከተተረጐሙት መካከል፣ ኀጢአት አንዱ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ኀጢአትን በማያሻማ ትርጉም፣ “የአንድ ሰው አለመታዘዝ” (ዘፍ. 3፥17፤ ሮሜ 5፥12፡ 15፡ 18፡ 19)፣ ከእግዚአብሔር ክብር መጉደል ወይም እግዚአብሔር ወዳሰበልን እውነተኛ ግብና ክብር አለመድረስ (ሮሜ 3፥23)፣ በራስ መንገድና ዝንባሌ መሄድ (ኢሳ. 53፥6)፣ ማመጽ (1ዮሐ. 3፥4) የሚሉና በሌሎችም ትርጉሞች በግልጥ ተርጉሞት እንመለከታለን።

Sunday, 3 May 2020

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፩)

Please read in PDF
   ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስና ቅዱሳን ደቀ መዛሙርት፣ ከእነርሱ መሄድ በኋላ ሐሰተኛ መምህራን ሊመጡ እንዳላቸው በግልጥ ተናግረዋል።  የሐሰት መምህራን ሁል ጊዜ የእውነተኛ ደቀ መዛሙርት አለመኖርን ይመኛሉ ወይም የእውነተኛ ደቀ መዛሙርትን ቸለተኝነት እንደ መግቢያ በር ይጠቀሙበታል።  ስለዚህም ሁልጊዜ ባለመታከት አንገታቸውን ከማስገግ አያርፉም።  አሳቻ ቦታ ቆመው ምቹ ጊዜ እንዲመጣላቸው ተግተው ይጠብቃሉ።

Sunday, 26 April 2020

በሕማሙና በትንሣኤው ዙርያ የነበሩ ምስክሮች (ክፍል አምስት)


3. ትንሣኤውን በመመልከት ኹሉን ትቀድማለች፦ ባለፉት ጊዜያት ጌታ መንፈስ ቅዱስ እንዳስተማረን፣ በመግደሎሟ ሴት ኹለት ነጥቦችን አንስተን፤ ሰባት አጋንንት ያወጣላትና እንዲሁም የጌታ ኢየሱስን ሕይወትና ትምህርት ተመልክታ፣ ፍጹም የተከተለችው መኾኑን አንስተናል። ከዚሁ ቀጥለን የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ምስክሮች ስለ ኾነችው ሴት በጥቂቱ እንመለከታለን።


Friday, 24 April 2020

ቅንነት ጥሎ፤ ዘፈን አንጠልጥሎ!

Please read in PDF
    ተኩላው ወደ በጐች ጐረኖ መሰስ ብሎ ሲገባ፣ ዝም ማለት ወይም ባላየ ማለፍ “ተለመደ”፤ የእግዚአብሔርን ምሕረት አስታክኮ፣ ኀጢአትን “ምን አለበት?” እያሉ ማላመድ የለቀቅተኛ ነገረ መለኮታዊያንና በሰልን ባይ አማኝና አገልጋዮች መገለጫ ኾነ፤ ኀጢአትን መጠየፍ አጉል አክራሪነት ተባለ፤ ኀጢአተኝነትን መካድና መቃወም ተቃዋሚነትና ከሳሽነት ተብሎ ተፈረጀ፤ ግብረ ሰዶማዊው አገልጋይ ሲሰብክ፣ “መጀመሪያ ንስሐ ግባ!” ማለት ግብዝነትና ማካበድ ኾነ፤ በተቃራኒው ደግሞ ዘፋኝነት ከመዝሙርነት ሲጣባ መንፈሳዊ ግልጋሎት፣ ኢየሱስን የሚጋርድ ተግባር ትክክል፣ የተሰቀለውን ክርስቶስ የሚሸቅጥ ተግባርና ዐሳብን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ለማድረግ ጥቅሶችን ማስጨነቅ ተወደደ፤ ተኩላውን ከመንጋው ማላመድ “ካውንስል” ተብሎ ተሞገሰ፤ ኢየሱስ ሳይኾን ቡድንና አገልጋይ ነኝ ባይ በሰው ልብ ገነነ፤ ለቀቅተኞች ቤተ ክርስቲያንን ንብ የማር ቀፎን እንደሚከብብ ከበቡአት። 

Wednesday, 22 April 2020

ተነሥቶአል!

Please read in PDF
ይህ ታላቅ ምስክር የተሰጠው ለታላቁ መሲህ ለክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ ነው፤ ሞት ብርቱ ሥጋ ለባሽን ኹሉ አሸንፎ ገዝቶአል፤ በጦር ሜዳ ጀግኖች የነበሩትን አርበድብዶ፣ “በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?” (1ሳሙ. 15፥32) በማስባል፣ በፊቱ አንበርክኮአል። ሞት ያልገዛው ብርቱ፣ ያልሻረው ኃያል፣ ያልጠቀለለው ጎበዝ፣ ያልዋጠው አለቃ፣ ያልሰበረው ጠንካራ … በምድር ላይ ከቶ አልነበረም። ሞት ወደቀውን ዓለም ተከትሎ፣ በሰው ልጆች ኹሉ ነግሦ ኖሮአል፤ “በአንዱም በደል ሞት በአንዱ በኩል” ወደ ሥጋ ለባሹ ዓለም ሰተት ብሎ ገባ፤ (ሮሜ 5፥17) እንዲል።


Friday, 17 April 2020

የሃይማኖት መሪዎች በኢየሱስ ላይ ለምን ተነሣሱ?

Please read in PDF
   በሰሙነ ሕማማት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሥጋ ሞቱ ይዘከራል፤ ስለ ሞቱ የተነገሩ ክፍሎች በብዛት ይነበባሉ፤ ይፈከራሉ፤ ይታተታሉ። በእነዚህ ጊዜያት አብዛኛውም የክርስቲያን ማኅበረ ሰብ “የፍለጋውን ዱካ” ወደ መንፈሳዊ ነገሮች ሲያደርግም ይታያል። መጠጥና ጭፈራ ቤቶች፣ የቁማር፣ የጫት መቃሚያና ሺሻ፣ ጋንጃ መማጊያ ቤቶች ከወትሮው ጊዜ በተለየ፣ ሰዎች ጐራ አይሉባቸውም[ኮቪድ 19 ኮሮና ጭርሱን ጠረቀመልን - እሰይ - ኡፈይ]። በሰሙነ ሕማማት የዘፈን ኮንሰርቶች፣ የመጠጥ ድግሶች ጨርሶ አይታሰቡም፤ ይህ ግን ከሳምንት ያላለፈ ጥንቃቄና መጠበቅ መኾኑን ስናስተውል፣ ነገሩ መንፈሳዊ ሳይኾን የግብዛዊነት ጠባይ መኾኑን እንረዳለን።