Thursday, 21 May 2020

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፭)

Please read in PDF


   ከዚህ ቀደም የስህተት መምህራን የማይነኳቸውን ሦስት ርዕሶችን ማለትም ኀጢአትን፣ ንስሐን፣ የእግዚአብሔርን ፍርድና ቊጣ መመልከታችን ይታወሳል፤ ዛሬ ደግሞ ቀጣዩን ርእስ እንመለከታለን።

4.
ስለ ቅድስና፦ ቅድስና በብሉይም ኾነ በአዲስ ኪዳን ውስጥ እጅግ የከበረ ዐሳብ ነው። በብሉይ ኪዳን በተለይም ከሕጉ መሰጠት በኋላ፣ ከቅድስና ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጠንካራው ቁልፍ ቃል፣ቅድስና ለእግዚአብሔርየሚለው ነው። ይህም በጥሩ ወርቅ በተሠራው አክሊል ላይ፣ እንደ ማኅተም ቅርጽ ተሠርቶ፣ ኹሉም ሰው ሊያየው በሚችል መልኩ፣ በራሱ ላይ አክሊሉን ይደፋዋል፤ (ዘጸ. 3930) በማኅተም ቅርጽ ያለውንቅድስና ለእግዚአብሔርየሚለውን ጽሕፈት ማንም ይሸሽገው ዘንድ አይችልም። ከእግዚአብሔር ጋር በመኾን፣ የተካፈልነውን ቅድስና እኛ ራሳችን እንኳ መሸሸግ አንችልም፤ ልክ ሙሴ የፊቱን ብርሃን መሸፈን እንዳልቻለው፤ (ዘጸ. 3429)

Sunday, 17 May 2020

የኅዳር በሽታ፤ ኮሮና፤ ዝሙት!

50 ሚሊየን በላይ ሕዝብ የቀጠፈው፣ ዓለም ዓቀፉ ብሪትሽ ፍሉ፣ በአገራችን ሲከሰት "የኅዳር በሽታ" መባሉንና የመጣበት ምክንያትም "ዘማዊ በምድሪቱ ስለ በዛ ነው" ተብሎ ይታመን እንደ ነበር ስንቶች ሰምተን ይኾን? [በእርግጥ በአገራችን አንድ ጥፋት ሲከሰት፣ ወዲያው ከመቅሰፍትና ከመዓት ጋር ማያያዙ የተለመደ ቢሆንም፣ በዚያ ዘመን ዝሙት የተስፋፋ መኾኑን በሚገባ ያሳብቃል] እግዚአብሔር ግን ምሕረቱ ብዙም፤ ለዘላለምም ነው!

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፬)

Please read in PDF

    3.  የእግዚአብሔርን ቊጣና ፍርድ አይናገሩም፦ ዓይን ያወጡ ሃሳውያን አገልጋዮች ብቻ ሳይኾኑ፣ በአከባቢያችን ያሉ አንዳንድ ለቀቅተኛ እንኳ፣ “የእግዚአብሔርን ፍቅር ብቻ ማውራት አይበቃምን?” ሲሉ፣ በተደጋጋሚ እንሰማቸዋለን። ነገር ግን ከተነገረውና በግልጥ ከተቀመጠው ከእግዚአብሔር ዐሳብ መራቅ አደጋ አለው፤ ደግሞም የመጽሐፍ ቅዱስን እውነተኛነትና አይሻሬነትን ማቃለል ነው።

Wednesday, 13 May 2020

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፫)

Please read in PDf

2.  ንስሐ፦ የስህተት መምህራን የማይነኩትና የማይደፍሩት ሌላው ርእስ ቢኖር ንስሐ ነው። ከእግዚአብሔር ለተለየው ዓለምም፤ በቤቱ ኖሮ ለሚበድለው አማኝም ንስሐ ዕለታዊ ተግባር ነው። በብሉይ ኪዳን ዐሳብ የአንድን ሰው ከኀጢአት ወደ እግዚአብሔር መመለስን የሚያመለክት ሲኾን (ኢሳ. 9፥13፤ ኤር. 4፥22፤ 5፥3፤ 26፥3፤ ሆሴ. 5፥4፤ 7፥10)፤ የአዲስ ኪዳን ምንባባት ደግሞ ኹለንተናዊ መመለስን የሚያመለክቱ ናቸው፤ ለምሳሌም፦ የነነዌ ሰዎች ኹለንተናዊ በኾነ ዝንባሌአቸው ንስሐ መግባታቸውን፣ “በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፥” በማለት ጌታ ኢየሱስ ተናገረ (ዮና. 3፥5-9፤ ማቴ. 12፥41)፣ ነነዌ ዮናስን ከተቀበለች፣ አይሁድም ከዮናስ የሚበልጠውን ጌታ አምነው ሊቀበሉ ይገባ ነበርና።

Saturday, 9 May 2020

Friday, 8 May 2020

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፪)

Please read in PDf

·        ኀጢአት፦ በስህተት መምህራን ዘንድ ትርጉማቸው ከተበላሹ ወይም እንደ ገና ከተተረጐሙት መካከል፣ ኀጢአት አንዱ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ኀጢአትን በማያሻማ ትርጉም፣ “የአንድ ሰው አለመታዘዝ” (ዘፍ. 3፥17፤ ሮሜ 5፥12፡ 15፡ 18፡ 19)፣ ከእግዚአብሔር ክብር መጉደል ወይም እግዚአብሔር ወዳሰበልን እውነተኛ ግብና ክብር አለመድረስ (ሮሜ 3፥23)፣ በራስ መንገድና ዝንባሌ መሄድ (ኢሳ. 53፥6)፣ ማመጽ (1ዮሐ. 3፥4) የሚሉና በሌሎችም ትርጉሞች በግልጥ ተርጉሞት እንመለከታለን።

Sunday, 3 May 2020

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፩)

Please read in PDF
   ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስና ቅዱሳን ደቀ መዛሙርት፣ ከእነርሱ መሄድ በኋላ ሐሰተኛ መምህራን ሊመጡ እንዳላቸው በግልጥ ተናግረዋል።  የሐሰት መምህራን ሁል ጊዜ የእውነተኛ ደቀ መዛሙርት አለመኖርን ይመኛሉ ወይም የእውነተኛ ደቀ መዛሙርትን ቸለተኝነት እንደ መግቢያ በር ይጠቀሙበታል።  ስለዚህም ሁልጊዜ ባለመታከት አንገታቸውን ከማስገግ አያርፉም።  አሳቻ ቦታ ቆመው ምቹ ጊዜ እንዲመጣላቸው ተግተው ይጠብቃሉ።

Sunday, 26 April 2020

በሕማሙና በትንሣኤው ዙርያ የነበሩ ምስክሮች (ክፍል አምስት)


3. ትንሣኤውን በመመልከት ኹሉን ትቀድማለች፦ ባለፉት ጊዜያት ጌታ መንፈስ ቅዱስ እንዳስተማረን፣ በመግደሎሟ ሴት ኹለት ነጥቦችን አንስተን፤ ሰባት አጋንንት ያወጣላትና እንዲሁም የጌታ ኢየሱስን ሕይወትና ትምህርት ተመልክታ፣ ፍጹም የተከተለችው መኾኑን አንስተናል። ከዚሁ ቀጥለን የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ምስክሮች ስለ ኾነችው ሴት በጥቂቱ እንመለከታለን።


Friday, 24 April 2020

ቅንነት ጥሎ፤ ዘፈን አንጠልጥሎ!

Please read in PDF
    ተኩላው ወደ በጐች ጐረኖ መሰስ ብሎ ሲገባ፣ ዝም ማለት ወይም ባላየ ማለፍ “ተለመደ”፤ የእግዚአብሔርን ምሕረት አስታክኮ፣ ኀጢአትን “ምን አለበት?” እያሉ ማላመድ የለቀቅተኛ ነገረ መለኮታዊያንና በሰልን ባይ አማኝና አገልጋዮች መገለጫ ኾነ፤ ኀጢአትን መጠየፍ አጉል አክራሪነት ተባለ፤ ኀጢአተኝነትን መካድና መቃወም ተቃዋሚነትና ከሳሽነት ተብሎ ተፈረጀ፤ ግብረ ሰዶማዊው አገልጋይ ሲሰብክ፣ “መጀመሪያ ንስሐ ግባ!” ማለት ግብዝነትና ማካበድ ኾነ፤ በተቃራኒው ደግሞ ዘፋኝነት ከመዝሙርነት ሲጣባ መንፈሳዊ ግልጋሎት፣ ኢየሱስን የሚጋርድ ተግባር ትክክል፣ የተሰቀለውን ክርስቶስ የሚሸቅጥ ተግባርና ዐሳብን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ለማድረግ ጥቅሶችን ማስጨነቅ ተወደደ፤ ተኩላውን ከመንጋው ማላመድ “ካውንስል” ተብሎ ተሞገሰ፤ ኢየሱስ ሳይኾን ቡድንና አገልጋይ ነኝ ባይ በሰው ልብ ገነነ፤ ለቀቅተኞች ቤተ ክርስቲያንን ንብ የማር ቀፎን እንደሚከብብ ከበቡአት። 

Wednesday, 22 April 2020

ተነሥቶአል!

Please read in PDF
ይህ ታላቅ ምስክር የተሰጠው ለታላቁ መሲህ ለክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ ነው፤ ሞት ብርቱ ሥጋ ለባሽን ኹሉ አሸንፎ ገዝቶአል፤ በጦር ሜዳ ጀግኖች የነበሩትን አርበድብዶ፣ “በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?” (1ሳሙ. 15፥32) በማስባል፣ በፊቱ አንበርክኮአል። ሞት ያልገዛው ብርቱ፣ ያልሻረው ኃያል፣ ያልጠቀለለው ጎበዝ፣ ያልዋጠው አለቃ፣ ያልሰበረው ጠንካራ … በምድር ላይ ከቶ አልነበረም። ሞት ወደቀውን ዓለም ተከትሎ፣ በሰው ልጆች ኹሉ ነግሦ ኖሮአል፤ “በአንዱም በደል ሞት በአንዱ በኩል” ወደ ሥጋ ለባሹ ዓለም ሰተት ብሎ ገባ፤ (ሮሜ 5፥17) እንዲል።


Friday, 17 April 2020

የሃይማኖት መሪዎች በኢየሱስ ላይ ለምን ተነሣሱ?

Please read in PDF
   በሰሙነ ሕማማት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሥጋ ሞቱ ይዘከራል፤ ስለ ሞቱ የተነገሩ ክፍሎች በብዛት ይነበባሉ፤ ይፈከራሉ፤ ይታተታሉ። በእነዚህ ጊዜያት አብዛኛውም የክርስቲያን ማኅበረ ሰብ “የፍለጋውን ዱካ” ወደ መንፈሳዊ ነገሮች ሲያደርግም ይታያል። መጠጥና ጭፈራ ቤቶች፣ የቁማር፣ የጫት መቃሚያና ሺሻ፣ ጋንጃ መማጊያ ቤቶች ከወትሮው ጊዜ በተለየ፣ ሰዎች ጐራ አይሉባቸውም[ኮቪድ 19 ኮሮና ጭርሱን ጠረቀመልን - እሰይ - ኡፈይ]። በሰሙነ ሕማማት የዘፈን ኮንሰርቶች፣ የመጠጥ ድግሶች ጨርሶ አይታሰቡም፤ ይህ ግን ከሳምንት ያላለፈ ጥንቃቄና መጠበቅ መኾኑን ስናስተውል፣ ነገሩ መንፈሳዊ ሳይኾን የግብዛዊነት ጠባይ መኾኑን እንረዳለን።



“ለይሁዳ ወልዱ ወውሉደ ወልዱ ይደምሰስ!” ለምን አንልም?

Please read in PDF
   በሰሙነ ሕማማት ከምናስተውለው አስደናቂ ነገር አንዱ፣ ይሁዳን የሚረግሙ ሰዎችና አብያተ ክርስቲያናት የመብዛታቸው ጉዳይ ነው። ለክርስቶስ ተላልፎ መሰጠት ይሁዳን ተቀዳሚ ተጠያቂ በማድረግ፣ ይሁዳንና ዘር ማንዘሩን የሚራገሙና የሚኰንኑ፣ የአምልኮ አካላቸውም አድርገው፣ የይሁዳን ኀጢአት ዘክረው፣ በብዙ የሚወቅሱ አያሌ “ክርስቲያኖች” አሉ። ክፋትን መጠየፍ አንድ ነገር ቢኾንም፣ ከእውነት ብዙ መራቅ ግን ግብዝነትን ያጐላል።


Wednesday, 15 April 2020

መሲሑ ሲደነግጥና ሲያጣጥር!

Please read in PDF
   ከኢየሩሳሌም ከተማ በቄድሮን ወንዝ ማዶ በደብረ ዘይት ግርጌ ባለው የአትክልት ስፍራ፣ ጌቴሴማኒ እየተባለ በሚጠራው ስፍራ፣ ሐሙስ ማታ፣ “የናዝሬቱ ኢየሱስ … በተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሔር ዘንድ … የተገለጠው ሰው” (ሐዋ. 2፥22)፣ “ሊያዝን ሊተክዝም ጀመር” (ማቴ. 26፥37)። ጌቴሴማኒ መልካሙና መሃሪው ጌታ ኢየሱስ ስቃዩን የጀመረበት ስፍራ ነው፤ ስለ ሰው ልጆች ኀጢአትና በደል፣ እርሱ የምድርና የሰማይ ሐዘንና ትካዜ በእርሱ ላይ ወረደ፤ በዚያም ሌሊት ብቻውን ተሳቀየ።
   

Sunday, 12 April 2020

ጌታ አኹን አድን

ስለ በዛው ጣዕር ስለ ሕፃናት ዋይታ
ስለ አዛውንቱ ስለ እናቶች እንባ
እንደ ቅጠል ረግፎ ቀብር በወረደው

Thursday, 9 April 2020

የ“ዲያቆን” አሸናፊ መኮንን፣ አዲሱ ድርሳነ ማርያም (ክፍል ፪ እና የመጨረሻ)

Please read in PDF

የወንጌሉን ዓላማ በመሳት፣ በአሸናፊ የተተረጐሙ “ትርጓሜያት”


1. የሰርጉ ተቀዳሚ ዓላማ “የእመቤታችንን የድንግል ማርያምን የእምነት ጸሎት ለማብራራት ነው”[1] የሚለው፣ የዮሐንስ ወንጌል ተቃራኒ ዐሳብ ነው። “ዲያቆን” አሸናፊ፣ እመቤታችን የጸለየችው ጸሎት ተራ ጸሎት አይደለም ቢልም፣ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ኹለት ውስጥ ጸሎት መኖሩን አናነብም ወይም ወንጌላዊው ዮሐንስ፣ ቅድስት ማርያም ጸሎትን መጸለይዋን አልጻፈልንም። ይህን ለማለት አስግጎ ወይም ወደ ቃሉ በማሰገባት የተረጐመው ክፍል፣ “የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት፦ የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም አለችው።” የሚለውን አንቀጽ ነው፤ (2፥3)።[2] ጸሎት ነው ከማለት ባለፈ፣ አስደናቂ ልመና፣ የቃና ዘገሊላው ጸሎት፣ የድንግል ጸሎት እያለ ሲያሞጋግሰው እናስተውላለን። ከዚሁ ጋር በተያያዘም ጸሎት ያለውን አንቀጽ፣ “እንደ ፈቃዱም የቀረበ፣ የጌታን ልብ ያወቀ ጸሎት” በማለትም ያሞካሸዋል።