Wednesday, 26 October 2016

ስለሁለተኛው ዛፍ

Please read ion PDF

ዛሬ ካነበብኩት መጽሐፍ እናንተም እንድትካፈሉ ወደድሁ፤ እናም ታነብቡት ዘንድ ይኸው ጋበዝኳችሁ፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ምሪት ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡ አሜን፡፡
መሪ
     አንባቢ ሆይ! በዚህ መጽሐፍ ከመጀመርያ እስከመጨረሻ ወደ ምሥራቅ  ሔድሁ፤ ወደምዕራብ ተመለስሁ፤ ወደሰሜን ሔድሁ፤ ወደደቡብ ተመለስሁ እያለ ተጽፎ ይገኛል፡፡ ምሥራቅ ሲል መጻሕፍተ ሐዲሳት ማለቱ ነው፡፡ ምዕራብ ሲል መጻሕፍተ ብሉያት ማለቱ ነው፡፡ ሰሜን ሲል የሊቃውንት መጻሕፍት ማለቱ ነው፡፡ ደቡብ ሲል አዋልድ መጻሕፍት ማለቱ ነው፡፡ ዓለም ያለ እንደሆመ ግን መጻሕፍትን ሁሉ ማለቱ ነው፡፡ ይህንም ካስታወቅሁ በኋላ ምሥራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ የሚለው ሀገር እንዳይመስላችሁ፡፡ እግዚአብሔር የልጁን የክርስቶስን ብርሃን በልባችሁ ውስጥ ያብራላችሁ፡፡ አሜን፡፡ ፪ጴጥ.፩፥ ፲፱፡፡
ዕራፍ ፪
ስለሁለተኛው ዛፍ
    ከዚህም በኋላ ወደምሥራቅ ሀገር ዞርሁ፡፡ በዚህም ሀገር፤ ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስ፣ ዮሐንስ፣ የሚባሉ ሰዎች ጌቶች ሆነው ይኖራሉ፡፡ ወደእነርሱም ደጅ የማይደርስ ሰው የለም፡፡
    እኔም ወደ እነርሱ ቤት ስሔድ በመንገድ ዳር አንድ ዛፍ አገኘሁ፡፡ ይህም ዛፍ በቁመትም፣ በመልክም፣ በፍሬም ያንን በመጀመርያ ያየሁትን ዛፍ ይመስላል፡፡ ዮሐ.፲፬፥፱፡፡

Wednesday, 19 October 2016

Thursday, 13 October 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና (ክፍል አምስት)

መጽሕፍ ቅዱስና ዘረኝነት
መጽሐፍ ቅዱስ ዘረኛነትን በግልጥ ይቃወማል፡፡ ምክንያቱም ፦
1.    ሁላችን ከጥንት አንድና እኩል ነበርን ፤ ነንም!
    እግዚአብሔር ከጥንት የሰው ልጆችን ያየው በአንዱ ሰው በአዳም በኩል ነው፤ የሰው ልጅ በኃጢአቱ የወደቀውና የተበላሸው በአንዱ በአዳም በኩል ነው፤ (ሮሜ.5፥12)፡፡ እንዲሁ ወደአዲስ ኪዳንም ብንመጣ እግዚአብሔር አለምን ሁሉ በምህረት አይኑ ያየው በአንድ ልጁ በኩል ነው ፤ ማለትም እንደአንድ ቤተ ሰብ የቆጠረን በደሙ በተጠራነው ጥሪ ነው፡፡
    በክርስቶስ አንድ ወደሆንነበት ቅድስት ሕብረት ለመሰባሰብ መስፈርቱም ማንነትና ዘር ሳይሆን አብርሃማዊ እምነት መያዝ በቂ እንደሆነ ታላቁ መጽሐፍ ይነግረናል፡፡ “እምነት የእግዚአብሔር ሥጦታ ነው፤ ከመንፈስ ቅዱስም ይገኛል፤ (ገላ.5፥23 ፤ ኤፌ.2፥8 ፤ 2ተሰ.2፥13)፡፡ ሰው በእምነት ይጸድቃል፤ (ሮሜ.3፥28 ፤ ገላ.2፥16) ነገር ግን በእምነት ከክርስቶስ ጋር ስለሚተባበር፥ እግዚአብሔርን ሥራ መሥራት ይጀምራል (ኤፌ.2፥8-10) ስለዚህ ሰው እውነተኛ አማኝ መሆኑ የሚጣወቀው በሥራው ነው”፡፡ [1]

Saturday, 8 October 2016

ኢትዮጲያ ሆይ! ላሁኑ ብቻ ያይደለ፥ ላለፈውም ጥፋትሽ ማቅ ለብሰሽ ንስሐ ግቢ!!!


   Please read in PDF

  አቤቱ የሰማይ አምላክ ሆይ፥ ለሚወድዱህና ትእዛዝህን ለሚያደርጉ ቃል ኪዳንንና ምሕረትን የምትጠብቅ፥ ታላቅና የተፈራህ አምላክ ሆይ፥ እኔ ባሪያህ ዛሬ በፊትህ ስለ ባሪያዎችህ ስለ እስራኤል ልጆች ሌሊትና ቀን የምጸልየውን ጸሎት ትሰማ ዘንድ ጆሮህ ያድምጥ፥ ዓይኖችህም ይከፈቱ፤ በአንተ ላይም ያደረግነውን የእስራኤልን ልጆች ኃጢአት እናዘዝልሃለሁ፤ እኔና የአባቴም ቤት በድለናል። እኛም በአንተ ላይ እጅግ ክፉ ሠርተናል ለባሪያህም ለሙሴ ያዘዝኸውን ትእዛዝና ሥርዓት ሕግም አልጠበቅንም። አሁንም ብትተላለፉ በአሕዛብ መካከል እበትናችኋለሁ፤ ወደ እኔ ብትመለሱ ግን ትእዛዜንም ብትጠብቁ ብታደርጓትም፥ ከእናንተ ሰዎች እስከ ሰማይ ዳርቻ ድረስ ምንም ቢበተኑ ከዚያ እሰበስባቸዋለሁ፥ ስሜም ይኖርበት ዘንድ ወደ መረጥሁት ስፍራ አመጣቸዋለሁ ብለህ ለባሪያህ ለሙሴ ያዘዝኸውን ቃል እባክህ አስብ። እነዚህም በታላቅ ኃይልህና በብርቱ እጅህ የተቤዠሃቸው ባሪያዎችህና ሕዝብህ ናቸው። ጌታ ሆይ፥ ጆሮህ የባሪያህን ጸሎት፥ ስምህንም ይፈሩ ዘንድ የሚወድዱትን፥ የባሪያዎችህን ጸሎት ያድምጥ፤ ዛሬም ለባሪያህ አከናውንለት፥ በዚህም ሰው ፊት ምሕረትን ስጠው።” (ነህ.1፥5-11)


      ልብ የሚሰብር ጸሎት የጸለየው የእግዚአብሔር ሰው ቅዱስ ነህምያ ነው፡፡ ነህምያ የስሙ ትርጓሜ “እግዚአብሔር ያጽናናል” ማለት ነው፡፡ በእውነትም ሕይወቱና ንግግሩ እግዚአብሔር ሕዝቡን ሊያጽናናበት የተጠቀመበት ምርጥ ሰው ነው፤ ነህምያ፡፡  ይህ ቅዱስ የእግዚአብሔር ሰው እጅግ የተወደደ፥ ለእኛም ብዙ ምሳሌና ልንማርበት የሚያስችል የቅድስና ሕይወት የነበረው ነው፡፡

Wednesday, 5 October 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና (ክፍል አራት)

Please read in PDF
የዘረኛ ሰዎች ባሕርያት
1.    ላውን የሚንቁ
      ዘረኛነት ባህርይው ራሱ “የእኔ ነገር ትልቅ ነው” የሚል ነገር በውስጡ አለበት፡፡ ንቀት ”እኔ ከሌላው እሻለለሁ ወይም እበልጣለሁ” የሚል ክፉ ሃሳብን ያዘለ ነው፡፡ ጀርመናውያን በይሁዲዎች ላይ ከመነሳታቸው በፊት ሲመለከቷቸው የነበረው በንቀት ነበር፡፡ በአገራችንም ያለውን እውነት ብናይ አንዱ ብሔር ሌላውን ብሔር ሲንቅ ያየንበት፤ የምናይበትም ጊዜ ብዙ ነው፡፡ በአንድ ወቅት የዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ ለሥራ ጉዳይ ወደአንድ ክልል ሄዶ ነበር፤ በዚያም መኪናችን ቆሽሻ ነበርና ልናሳጥብ ወደአንድ መኪና ማሳጠቢያ ገባን፤ የመኪናችንን ታርጋ ብቻ አይተው በሚጠየፍ ማንነት ነበር አጣቢዎቹ የተመለከቱን፤ ሊያጥቡልንም ፈቃደኞች ስላልነበሩ ትተን ሄድን፡፡ በጥቆማ ግን ወደሌላ ሥፍራ ሄደን አሳጥበናል፡፡ ያጠበልን ልጅም ግን “የታርጋው አከባቢ ነዋሪ” እንደነበር በኋላ ላይ ሰማን፡፡

Wednesday, 28 September 2016

የጳጳሱና የሰባክያኑ ቤተ ክርስቲያንን “መለካዊ” የማድረግ ሃሳባቸው እስከምን ድረስ ነው?!

Please read in PDF      

          ነቢየ እግዚአብሔር ኤርምያስ በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች ዘንድ “አልቃሻው ነቢይ” ተብሎ ይጠራል፡፡ ይህንንም ስያሜ ያገኘበት ዋናው ምክንያት፥ ሕዝቡ በኃጢአትና በነውር ምድሪቱን እጅግ በማርከሳቸውና ፊታቸውን ወደንስሐ ዘወር እንዲያደርጉ፥ ከእነርሱ ጋር እየተራበና እየተጠማ በመካከላቸው ሆኖ አዘውትሮ ቢናገራቸውም፥ እስራኤል ሊሰሙት ካለመውደዳቸው ባሻገር አጥብቀው ስለተቃወሙትና ሊቀበሉት ፈጽመው ስላልወደዱት ነው፡፡
    በዚህም ምክንያት በጥልቅ ሐዘን መዋጡን፥
    “አንጀቴ! አንጀቴ! ልቤ በጣም ታምሞአል፥ በውስጤም ልቤ ታውኮብኛል፤ ነፍሴ ሆይ፥ የመለከትን ድምፅና የሰልፍን ውካታ ሰምተሻልና ዝም እል ዘንድ አልችልም፡፡ … ሕዝቤ ሰንፈዋልና አላወቁኝም ሰነፎች ልጆች ናቸው፥ ማስተዋልም የላቸውም፤ ክፉ ነገርን ለማድረግ ብልሃተኞች ናቸው፥ በጎ ነገርን ማድረግ ግን አያውቁም፡፡”፤ (ኤር.4፥19-22)፤ “ተወግተው ስለ ሞቱ ስለ ሕዝቤ ሴት ልጅ ሰዎች ሌሊትና ቀን አለቅስ ዘንድ ራሴ ውኃ፥ ዓይኔም የእንባ ምንጭ በሆነልኝ! ሁሉም አመንዝሮች፥ የአታላዮች ጉባኤ ናቸውና ሕዝቤን እተዋቸው ዘንድ ከእነርሱም እለይ ዘንድ በምድረ በዳ የመንገደኞች ማደሪያን ማን በሰጠኝ? ምላሳቸውን ስለ ሐሰት እንደ ቀስት ገተሩ፤ በምድር በረቱ ነገር ግን ለእውነት አይደለም፤ ከክፋት ወደ ክፋት ይሄዳሉና እኔንም አላወቁምና፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ ወንድምም ሁሉ ያሰናክላልና፥ ባልንጀራም ሁሉ ያማልና እናንተ ሁሉ ከባልንጀሮቻችሁ ተጠንቀቁ፥ በወንድሞቻችሁም አትታመኑ፡፡ ሰውም ሁሉ ባልንጀራውን ያታልላል በእውነትም አይናገርም፤ ሐሰትን መናገርንም ምላሳቸው ተምሮአል፥ ክፉንም ለማድረግ ይደክማሉ፡፡”(9፥1-5)፤ “እረኞች ሰንፈዋልና፥ እግዚአብሔርን አልጠየቁትምና አልተከናወነላቸውም፥ መንጎቻቸውም ሁሉ ተበትነዋል፡፡”(10፥21)፤ “ስለ ነቢያት፤ ልቤ በውስጤ ተሰብሮአል አጥንቶቼም ሁሉ ታውከዋል፤ ከእግዚአብሔር የተነሣ ከቅዱስ ቃሉም የተነሣ የወይን ጠጅ እንዳሸነፈው እንደ ሰካራም ሰው ሆኛለሁ፡፡ ምድር ከአመንዝሮች ተሞልታለችና፥ ከመርገምም የተነሣ ምድር አልቅሳለች፤ የምድረ በዳ ማሰማርያ ደርቆአል፤ አካሄዳቸው ክፉ ነው፥ ብርታታቸውም ቅን አይደለም፡፡ ነቢዩና ካህኑም ረክሰዋልና፥ በቤቴም ውስጥ ክፋታቸውን አግኝቻለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡” (23፥9-11)
የሚለው የነቢዩ ንግግር የሚያየው የእስራኤል ክፋት ምን ያህል እንዳቆሰለውና እንዳሳዘነው በትክክል ይገልጠዋል፡፡

Tuesday, 20 September 2016

በዘመን መለወጫ የተቀማጠለው ንጉሥ (የመጨረሻ ክፍል)

  please read in PDF

ልንመርጥ የምንችለው አንድ መንገድ ብቻ ነው፤ ከኃጢአትና ከጽድቅ መንገድ አንዱን፡፡ ከሁለቱ አንዱን እንጂ ለሁለቱም ማመቻመች አንችልም፡፡ “ከኃጢአት ጋር እየተጋደላችሁ ገና ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ አልተቃወማችሁም፤” (ዕብ.12፥4) የሚለው ቃል በእውነት ላይ እስከመጨረሻ አለመጽናትንና አለመጨከንን የሚያሳይ ነው፡፡ ለእውነት ከቆምን እስከሞት ድረስ እንጂ ሁለቱን ለማደላደል መሞከር ከውርደት አያድነንም፡፡
    የሳሙኤልን መጽሐፍ የጻፈው ጸሐፊ፥ በንጉሥ ዳዊት ሕይወት የሆነውን ውድቀት ሁሉ ምንም ሳያዛንፍ ነው፡፡ አስቡ! የነቢዩ ሳሙኤልን ሕይወት፥ “እነሆኝ በእግዚአብሔርና እርሱ በቀባው ፊት መስክሩብኝ የማንን በሬ ወሰድሁ? የማንንስ አህያ ወሰድሁ? ማንንስ ሸነገልሁ? በማንስ ላይ ግፍ አደረግሁ? ዓይኖቼንስ ለማሳወር ከማን ጋር እጅ ጉቦ ተቀበልሁ? እኔም እመልስላችኋለሁ፡፡ እነርሱም፦ አልሸነገልኸንም፥ ግፍም አላደረግህብንም፥ ከሰውም እጅ ምንም አልወሰድህም አሉ፤” (1ሳሙ.12፥3-4) በማለት ገልጦታል፡፡ እንዲሁ የዳዊትን ደካማና ኃጢአተኛ ሕይወት ሳያቅማማ ነው የገለጠው፡፡

Wednesday, 14 September 2016

... አዲስ ዘመን የለም



ቢግተለተል ዕድሜ፥ ምን ቢረዝም ዘመን፤
ተቆጥሮ ተሰልቶ፥ ቢሰጠን ብዙ ቀን፤

Friday, 9 September 2016

በዘመን መለወጫ የተቀማጠለው ንጉሥ (ክፍል አንድ)


Please read in PDF

እንኳን ለንስሐ የሚሆን ዘመን  ተጨመረላችሁ!!!
     ቅምጥልነትን፥ ቅዱስ ጳውሎስ “ቅምጥሊቱ ግን በሕይወትዋ ሳለች የሞተች ናት” (1ጢሞ.5፥6) በማለት ይገልጠዋል፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት መሞትን በሕይወት ቆሞ መሄድ አይተካውም፡፡ መንፈሳዊ ሞት ወደር የለሽ እጅግ አስጨናቂ ሞት ነው፡፡ ቆሞ በመሄድ ማማር የለም፤ በቁም “በውጭ አምረው የሚታዩ” ሁሉ ደመ ግቡዎች አይደሉም፤ ውስጣቸው “ርኩሰትም ሁሉ የተሞሉ በኖራ የተለሰኑ መቃብሮችን ሊመስሉ ይችላሉና”፤ (ማቴ.23፥27)፡፡ እንዲህ ያሉ ሰዎች በሕይወት የሞቱና ሕያውና የሚያድን ድምጽ መስማት የሚያስፈልጋቸው ናቸው፡፡
     ጌታችን “ሙታናቸውን እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው፤ አንተስ ሄደህ የእግዚአብሔርን መንግሥት ስበክ” (ሉቃ.9፥60) በማለት የተናገረው፥ በመንፈስ ሙት የሆኑ በሥጋ ሙት የሆኑትን ሊቀብሩ እንዳሉና በመንፈስ ሕያው የሆነ ግን የእግዚአብሔርን መንግሥት በብርታት ማገልገልና መስበክ እንዳለበት አጽንቶ ሊናገር ወዶ ነው፡፡ አስተውሉ! ጥቂት ቅምጥልነት ለምን አይነት መንፈሳዊ ሞት አሳልፎ ሊሰጠን እንደሚችል፡፡
   ንጉሥ ዳዊት ሁሉንም “ጠላቶቹን” ቢያሸንፍም፥ አሞናውያንን [1] ግን ገና አላሸነፈም ነበር፤ (2ሳሙ.10፥19)፡፡ እኒህ የቀሩ ጠላቶች ቢኖሩትም ግን፥ “እንዲህም ሆነ፤ በዓመቱ መለወጫ ነገሥታት ወደ ሰልፍ በሚወጡበት ጊዜ፥ ዳዊት ኢዮአብን ከእርሱም ጋር ባሪያዎቹን እስራኤልንም ሁሉ ወደጦርነቱ ሰድዶ ለራሱ ግን በኢየሩሳሌም ቆየ፤” (2ሳሙ.11፥1) አመሻሽ ላይ በዚያ ምቹና ተስማሚ ሰገነት ላይ (1ሳሙ.9፥25) ዳዊት ይመላለስ ነበር፡፡ በሌላ ንግግር ወደዳዊት ሕይወት ቅምጥልነት ሰተት ብሎ ገባ ማለት ነው፡፡ “በልክ መዝናናት” አንድ ነገር ነው፤ ለሥጋዊ ተድላና ለቅምጥልነት ተዘልሎ መቀመጥ ግን ራስን በወጥመድ ውስጥ የማስገባት ያህል እጅግ አደገኛ ነው፡፡

Sunday, 4 September 2016

የኢትዮጲያ “መካከለኞች” ወዴት ናቸው?

Please read in PDF     

       ቺቸሮ “አለመግባባት መፍትሄ የሚያገኘው በሁለት መንገዶች በውይይት ወይም በኃይል ነው፡፡ የመጀመርያው የሰው ባሕርይ ሲሆን ሁለተኛው የአራዊት ነው” ይላል፡፡ ባለመታደል ሁላችንም ሁለተኛውን መረጥን፡፡ ማሸነፍ እንጂ መሸነፍን ያለመቀበል እንደባህል አድርገን በመያዛችንና በሃገሪቱ የፖለቲካ ልምድ ካለመኖር ጋር ተዳምሮ የኢትዮጲያ ተራማጆች ኃይልን መርጠው በመንቀሳቀሳቸው የደም መፋሰሱንና የጥፋቱን መጠን በማባባስ ለሃገር ግንባታ ይውል የነበረ ወጣት ለቅስፈት ተዳርጓል፡፡ (ሌ/ኰሎኔል ፍሥሐ ደስታ፤ አብዮቱና ትዝታዬ ፤ 2008 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ፤ ፀሐይ አሳታሚ ድርጅት)

       ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለ ማርያም “እርምጃ እንዲወሰድ ከማዘዛቸው” በፊትም ሆነ በኋላ፥ የሕዝብ ኩርፊያ አሁንም ጋብ ያለ አይመስልም፡፡ ሕዝብ እንደሚናጠቅ የአንበሳ ደቦል “በገዛ ወገኑ” [እርስ በራሱ] ላይ ያደባ ይመስላል፤ “መንግሥት ሆይ!  ችግር አለብህ፤ ተስተካከል” ለማለት እየሄደበት ያለው አቅጣጫና አንዳንዶች እንደሚሉት ሕዝቡን የሚመራው “ሦስተኛው አካል” ዓላማና ግቡ ምንም እንደሆነ በትክክል አለመታወቁ ነገሮች የበለጠ እንዲወሳሰቡ ያደረገ ይመስላል፡፡
     እርግጥ ነው፥ የአብዛኛው ሰው ስሜት ሲደመጥ፥ “ይኼ መንግሥት በቃው፤ ይውረድ” ይመስላል፡፡  ይህ አካሄዱ ግን ፍጹም ኢ መንፈሳዊነት ብቻ ሳይሆን ኢ ሰብዓዊነት፣ ኢ ሥነ ምግባራዊነትና ኢ ሞራዊነት የሰፈነበት መሆኑ ነገሩን አስጨናቂና እጅግ አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡ ምንድር ነው አስጨናቂና አሳሳቢ የሚያደርገው? ብንል፦
1.     ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ምን ሆነው? በማን ላይ ነው እርምጃ እንዲወሰድ አዝዣለሁ ያሉት? ከእርምጃው በፊት ማወያየትና ማነጋገር አይቀድምም ወይ? ምክር አይፈለግም ወይ? እርምጃ የመጀመርያ ደረጃ መቀራረቢያና መግባቢያ መንገድ ነው ወይ? ሕዝብን ማድመጥና ፍላጐቱን መጠየቅ አይገባም ወይ? በደፈናው ከመፈረጅ ጥንተ ምክንያቱን ማጥናት፤ መረዳት አይገባም ወይ? ወይም ለምንድነዉ መንግስት በፖለቲካ አቅጠጫ ማሸነፍ የተሳነው? የሚሉና ሌሎች ብዙ ጥያቄዎችን መምዘዝ ይቻላል፡፡

Saturday, 27 August 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና (ክፍል ሦስት)

በእኛ መካከልስ ምን ይመስል ነበር?
   ዘረኛነትን በተመለከተ ከአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ብንነሳ፥ ኢትዮጲያ ከሰማንያ አራት በላይ ብሔረሰቦች የሚኖሩባትና በተለያየ ብዙ ቋንቋዎችም የሚነጋገሩ ሕዝቦች ያሉባት አገር ናት፡፡ አንዱ አንዱን ለመብለጥ ምክንያት የሚመስሉ ብዙ ነገሮች አሉ፤ ሰዎች ከአንድነት ይልቅ በየራሳቸው ነገር ላይ ትኩረት ሲያድርጉ ሳያውቁት ሌላውን በመጻረር የሚቆሙበት ጊዜም ብዙ ነው፡፡ ሰዎችን ወደሌላ የክህደት መንገድ ለመምራት መጽሐፍ ቅዱስን ሲያጠኑ በዚያው የመጽሐፍ ቅዱስ አማኝ ሆነው የቀሩ ሰዎች ያሉትን ያህል፤ መጽሐፍ ቅዱስን ተጠግተው ለራሳቸው ምስክርነት እየፈለጉ በዘረኛነት ክፉ ኃጢአት የተያዙ ብዙ ናቸው፡፡
    መጽሐፍ ቅዱስን ተገን ተደርጐ የሚሠራ ኃጢአት እጅግ አስከፊ ኃጢአት ነው፤ በእኛ መካከል ያለው የዘረኛነት መንፈስ እንዲህ ያለ ነው ብንል ማጋነን አለበት አያስብልም፡፡ አንድ ሃይማኖት የተወሰኑ ወይም የአንድ ብሔር እስኪመስል ወይም እስኪባል ድረስ በመካከላችን የሚታየው ነገር አስነዋሪ ነው፡፡ ይህንን በአንድ ጽሑፍ፦
“ … አሁን አሁን ነገራችን እንደዖዝያን ለምጽ ሊሸፈንበት ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ ራሱ ችግሩም “አለሁ፣ አለሁ” ብሏል፡፡  የለህም ብንለውም ራሱን በራሱ ያስመሰክራል፡፡ ሙስናው ፣ የዘመድ አሠራሩ …ወዘተ አግጥተው ወጥተዋል፡፡” [1]

Monday, 22 August 2016

በአዲስ አበባ፥ ምነው በሰበበ “ሰላማዊ ሰልፍ” ሁከት አልተቀሰቀሰም?!

Please read in Pdf 
የኢዮአታምን ምክር የማይሰማ ሕዝብና መሪ መጨረሻው ጥፋት ነው!!!
     ትላንት ማምሻውን ስልኬ ከወደብዙ ቦታ በተደረገላት ጥሪዎች ስትንጫረር ነበር፡፡ ከ“ክፍለ አገር” እና ከውጪው ዓለም፡፡ “አዲስ አበባ ሰላም ዋለችን? ከመገናኛ ብዙኃን ምንም መረጃ አጣን? ምንም ሁከት ወይም ሰላማዊ ሰልፍ አልነበረም? ... ምንም ምን አልነበረም? ... ” የሚሉና ሌሎች ጥያቄዎችን የሚጠይቁ ወንድሞችና እህቶች፡፡
     ከዚህ የጥያቄ ግርፍ በኋላ ለረጅም ሰዓት ቆም ብዬ ማሰላሰል ጀመርኩ፡፡ ሰው ከሰላም ይልቅ “ሰላማዊ ሰልፍ” ለምን ተጠማ? ከጸጥታ ይልቅ ግርግርና ሁከት ለምን መረጠ? የማያስማማ፣ የማያነጋግር፣ የማያወያይ፣ ጅምር ላይ ሆነን ፍጻሜ መተለም የማያስችል ክፉ መንፈስ ከወዴት ይሆን የተጣባን? የቀደመው ዘመን ታሪክ ስለምን መማርያ አልሆነንም? ከዚህ ቀደም የ“ንጉሠ ነገሥቱን” ሥርዓት ሰለቸን ብለን፥ ከአርባ ዓመት በላይ “የመራንን” ንጉሥ አዋርደን፣ ከሰውነት ተራ አውጥተን፣ “ለባዕድ” የማይነፈገውን የቀብር ቦታ እንኳ ለ“ንጉሠ ነገሥቱ” ነስተን፣ ስም አጠራሩን አጥፍተን ... ወታደራዊውን መንግሥት “በእልልታ በሆታ” በራሳችን ላይ ሾምን፡፡
እርሱም የዘራነውን አሳጨደን፡፡

Thursday, 18 August 2016

በዓይናችን አይተን!

Please read in PDF


ተረት መች ሆነና ብልሐታዊ ንግርት፣
የምሰብከውና የምንዘምርለት፣
አጉል ፍልስፍና ጥበብ መሰል ነገር፣

Tuesday, 16 August 2016

የኢትዮጲያ የ“ማስተዋል” ጸሐይ ምነው አዘቀዘቀ?



Please read in PDF


መንግሥት ሆይ! እባክህ ከማሰር ፤ ከማጐር ይልቅ፥ ራራ! ይቅር በል! ማር!!!
     በምዕራቡ ዓለም በተደላደለ መኖሪያ ቤታቸው ተቀምጠው እንደሰበኩን፥ “ጨካኝ ፣ እብሪተኛ ፣ አምባገነን ፣ አረመኔ ፣ ጉበኛ ፣ ዘረኛ ፣ ሴሰኛ ፣ አድርባይ ፣ አፋኝ …” ያሉት ይህ የአገር ቤቱ መንግሥት ወረደ እንበል፤ ግን እኒህ ዲያስፖራ ፖለቲከኞችና ፈሪሳውያን ሃይማኖተኞች ያልመለሱልን ጥያቄ፥ “ማን እንዲመራን ነው ያቀዱት? ፣ ማንን ይሆን ያዘጋጁልን? እነርሱ ራሳቸው ከአውሮፓና ከአሜሪካ ሊመጡና ሊመሩን? ፣ ወይስ ከዚሁ አገር ቤት የሚያሰናዱልን ነገር ኖሮ ይሆን?”
     አንድ ሌላ ጥያቄ አለኝ? እኒህ “ዲያስፖራውያን የፖለቲካና የሃይማኖት ዲስኩረኞች” ለመሆኑ ስለአንድነትና ስለመንፈስ አንድነት ለማውራት በእውኑ ሞራሉና ብቃቱ አላቸው? በአንድ ነገር አምናለሁ ፤ የአገር ቤቱ መንግሥት ብዙ ነውር ፣ ዕድፍ ፣ ርኩሰት ፣ ልክፍት ፣ በደል … አለበት ፤ ይህን አምናለሁ፥ አልጠራጠርም፡፡ አንድ ብርቱ መከራከርያ ግን አለኝ፡፡ ከአገር ቤቱ መንግሥት ይልቅ “የአሁኑን የነውጥ እንቅስቃሴ እየመራ ያለው የዲያስፖራው ጐልማሳ” ግን ነውሩና ርኩሰቱ ከአገር ቤት መንግሥት ይበልጣል ባይ ነኝ፡፡