Friday, 6 October 2023

በአጭሩ፣ ኢሬቻ የዋቄፈታ አማኞች አምልኮአዊ በአል ነው!

Please read in PDF

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ የሮማ ቄሳራውያን ያህል፣ ለባህላዊ ሃይማኖት መስፋፋት ታላቅ አስተዋጽዖ ያደረገ አካልን መጥቀስ አይቻልም። በተለይም እኒህ ነገሥታት ክርስቲያኖችን ለማጥፋት ከተጠቀሙበት መንገድ አንዱ፣ ራሳቸውን እንዲመለኩ በማቅረብና ጣዖታትን እንዲመለኩ አዋጆችን በማውጣት ነው፤ የሚቃወሙአቸውን ኹሉ ደግሞ ያለ አንዳች ርኅራኄ በመፍጀት ተካካይ የላቸውም።[1] የኢየሱስን ጌትነት አውጀው፣ የቄሳራውያንን አል ጌትነት መቃወምና ጣዖታትን ፍጹም መጠየፋቸው ለክርስቲያን ወገኖች ብርቱ የስደትና የሰማዕትነት ዋና ምክንያት ነበር።[2] በተለይም በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ የቤተ ክርስቲያን የስደት ዘመን ወይም ዘመነ ሰማዕታት በመባል የተጠራበት አንዱ ምክንያት፣ የክርስቲያኖች ቄሳራዊ አምልኮን፣ ሮማዊና ሌሎችንም ባህላዊ ሃይማኖቶችን መጠየፋቸውና አለመቀበላቸው ነበር።[3]

Wednesday, 4 October 2023

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፫)

 Please read in PDF

ካለፈው ቀጠለ …

3.3. የፍጥረት ዐላማን መረዳት

እግዚአብሔር፣ በማይቀየረውና ሊለወጥ በማይችለው (ሐ.ሥ. 2፥23)፣ በዘላለም ዕቅዱ (ኤፌ. 3፥10-11)፣ ፍጥረትን የፈጠረው ለራሱ ክብርና ዓላማ ነው። ለራሱ ዓላማ ስለ ፈጠረውም፣ ፍጥረት ክብሩን ያውጃል፤ (ኢሳ. 43፥6-7)። ለዚህም ነው፣ መጽሐፍ ቅዱስ፣ የእግዚአብሔርን ኅልውና ሲያስረዳ፣ “በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።” በማለት ስለ እግዚአብሔር ማብራሪያ ባለመስጠት፣ የፍጥረትን መፈጠር አስደናቂ ተግባር በመተረክ የሚጀምረው። ፍጥረትም የተፈጠረበትን ዓላማ ስለሚያውቅ፣ እግዚአብሔርን ገልጦ ያሳያል፤ ለፈቃዱም በግልጥ ይታዘዛል።



Wednesday, 20 September 2023

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፪)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

2.4. እውነትን በመኖር ለማደግ

እውነተኛ ዕውቀት አእምሮን ጤናማ ያደርጋል። እውነተኛ ዕውቀትና ጤናማ ትምህርት የሌላቸው ሕይወታቸውና ልምዳቸውም ጤናማ ሊኾን አይችልም። በክርስትና ትምህርት ስናውቅ እናምናለን፤ ስናምነው ደግሞ የምናውቀው ብዙ አለን። የእምነት ዕድገት የሕይወት፣ የአምልኮና የመንፈሳዊ ዕድገት ለውጥ ነው።

ቅዱስ ጳውሎስ፣ “የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።” (ኤፌ. 1፥17) በማለት፣ እግዚአብሔርን በማወቅ እንዲያድጉ የጥበብና የመገለጥ መንፈስ እንዲሰጣቸው ልመና ያቀርባል። ይህም ዕውቀት ከራሱ ከእግዚአብሔር እንጂ ከሌላ ከማንም ሊመጣ እንደማይችልም ጭምር ይናገራል።

Saturday, 16 September 2023

ጥንቆላና ሃይማኖተኝነት!

 Please read in PDF

ከሰሞኑ የስልጤ አከባቢ ጉዳይ አስደምሞኛል። አንድ ቤተ እምነት “በጥንቍልናና መተት፤ በድግምት አማኞቼን ወይም ተከታዮቼን አጥቅተውብኛል” በሚል አስባብ፣ በኦርቶዶክሳውያንና በወንጌላውያን አማኞች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን በምስልም፣ በድምጽም፣ በምስለ ወድምጽም ተመልክቻለሁ።

Monday, 11 September 2023

“ንስሐ ግቡ” (ማቴ. 3፥2)

 

መጥምቁ ዮሐንስንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ከሚያመሳስላቸው የስብከት ርዕሶች ቀዳሚው፣ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ” የሚለው መንግሥተ ሰማያዊ አዋጅ ነው። ቅዱስ ማቴዎስ ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ሲናገር፣ “በዚያም ወራት … በይሁዳ ምድረ በዳ እየሰበከ መጣ። የስብከቱም ማዕከል የእግዚአብሔር መንግሥትና ንስሐ ነበር። “ንስሐ” ድርጊታዊ ትርጒሙን ስንመለከት፣ “መመለስ” ማለት ነው። ይህም ከክፉ ድርጊቶች ኹሉ መመለስ፣ ክፉ ድርጊትን ኹሉ መተው፣ ከክፉ መንገድ ኹሉ ዘወር ማለትና ወደ ክርስቶስ መመለስ የሚል ትርጒምን የያዘ ነው።

Friday, 25 August 2023

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፩)

 Please read in PDF

ስመ ሥላሴ ለአማኞች የነገር መጀመሪያም፤ የነገር መጨረሻም ነው፤ “በስመ አብ …” ብሎ የጀመረ አማኝ፣ “ስብሐት ለአብ …” ብሎ መጨረሱ እውነትም፤ እምነትም ነው። ለዚህ ደግሞ ቅዱሳት መጻሕፍት ታላቅ ዋቢ፤ ምስክርም ናቸው። “ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።” (2ቆሮ. 1፥2) ብለው ጀምረው፣ “የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።” (2ቆሮ. 13፥14) ብለው መጨረሳቸው እምነትም፤ የእምነታችን ልምድም ነው።

Wednesday, 23 August 2023

አጵሎሳውያንም፤ ጳውሎሳውያንም ወደ ኢየሱስ ኑ!

 Please read in PDF

በዘመናችን አገልጋዮችን ማበላለጥ፣ አንዱን አገልጋይ “ጌታ” ሌላውን “ምንዝር” አድርጐ ማቅረብ ልክ እንደ ጳውሎስ ዘመን ያገጠጠ እውነት ነው። አማኞች የማንም እንዲኾኑ አልተጠሩም፤ በክርስቶስ የተዋጁ አማኞች የክርስቶስ ብቻ እንዲኾኑ የእግዚአብሔር የዘለዓለም ፈቃዱና ዕቅዱ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ፤ ቀና በሚመስል አመለካከት “እኔ የእገሌ ነኝ” የሚሉትን “እሰይ አበጃችሁ” ሲል አንመለከትም።

Tuesday, 22 August 2023

የክርስቶስን ትንሣኤ ጥቅሞች

 Please read in PDF

ከሙታን መካከል ስለ መነሣቱ፣ ቅዱሳት መጻሕፍት በምልዓት የሚመሰክሩት ስለ አንዱ ብቻ ነው፤ እርሱም ክርስቶስ ኢየሱስ። ከክርስቶስ በቀር ከሙታን መካከል የተነሣ እንደ ሌለ ከቅዱሳት መጻሕፍት ባሻገር፣ ሌሎችም መጻሕፍትም በድፍረት ይመሰክራሉ፤ “ስለዚህም ጌታ … በፈቃዱ ሞተ፤ ከተነሣም በኋላ ዳግመኛ አይሞትም፤ ከትንሣኤው በኋላ ግን ጌታ ይህን አልተናገረም፤ ከሰውም ወገን ማንንም ተነሥ፤ ከመቃብር ውጣ አላለም፤ ዳግመኛ እስከሚመጣባት ቀን ድረስ ለሰዎች ኹሉ አንድ ኾነው በሚነሡበት ቀን ሙታን ይነሣሉ አላቸው።” (ሃይማኖተ አበው ዘኤጲፋንዮስ፤ 1988 ዓ.ም፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ ምዕ. 59 ክፍል 13 ቊ. 49 ገጽ 209)።

Saturday, 19 August 2023

የጻድቅን ነፍስ የሚሹ ደም አፍሳሾች!

Please read in PDF

“ዶክተር” መስከረም ትባላለች፤ በደቂቀ እስጢፋኖሳውያን ዙሪያ ስለ ተናገረችው “ፈጠራ ክስ” እጅግ ጥቂት ነገር ማለት ወደድኹ። ... ከጥንት ጀምሮ ደቂቀ እስጢፋኖሳውያን ላይ የማያባራ የስም ማጥፋትና የዓመጽ ውሸት ይሰነዘራል። ምናልባት ግን እንደ ማኅበረ ቅዱሳንና ተከታዮቻቸው፣ ደቂቀ እስጢፋኖስን የሚፈራና በእነርሱ ታሪክ ራሱን አስገብቶ ጻድቅ ሊያደርግ የሚሻ ያለ አይመስለኝም። እስጢፋኖሳውያን ትምህርታቸው የጠራ፣ ሕይወታቸው የተመሰከረ ለመኾኑ ለዘመናት ተዳፍኖ፣ እግዚአብሔር በጊዜው በገለጠው ገድላቸው ላይ በትክክል ሰፍሮ አያሌ አጥኚዎችንና ኦርቶዶክሳውያንን እጅ በአፍ አስጭኖ አስደንቆአል።

Friday, 18 August 2023

ከኢየሱስ በቀር!

 Please read in PDF

የሙሴ ፍለጋ የኤልያስ ናፍቆት

የአበው ነቢያት ረሃብና ጥማት …

Sunday, 6 August 2023

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፳፭)

Please read in PDF

በባለፉት ጊዜያት፣ የ“መድሎተ ጽድቅ” ጸሐፊ፣ የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣን በተደጋጋሚ የሚቃወምበትንና የሚጥስበትን መንገድ እያሳየን መቆየታችን ይታወሳል። ዛሬም ጸሐፊው እንዴት ባለ መንገድ የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣን እንደሚጥስና እንደማያከብር ማሳየት እንቀጥላለን።

1.4.    አዋልድ[1] መጻሕፍትን እንደ መጻሕፍተ መለኮታውያት ማቅረብ ወይም ቅዱሳት መጻሕፍትን በአዋልድ መጻሕፍት ለመተርጐም ማሰብ፦ የ“መድሎተ ጽድቅ” ጸሐፊ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ከዚህ ቀደም እንደ ተናገርነው፣ የሕይወት ቃልን በብቻነቱ መያዙን አይስትም፤ ግን ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ ያሉት የሕይወት ቃላት ለማዳን፣ የዘላለም ሕይወት ለመስጠት፣ እውነተኛ የቅድስናና የማናቸውም መልካም ነገሮች ኹሉ መለኪያና መመሪያዎች ለመኾናቸው በቂዎች ናቸው ብሎ አያምንም።

Monday, 31 July 2023

ቅልወጣ የማይርቀው “ሃይማኖታችን”ና ፖለቲካ

 Please read in PDF

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሐዳስያን ከምትወቀስባቸው “ወቀሳዎች” አንዱ፣ ከፖለቲካው ወይም ከቤተ መንግሥት ጋር የነበራት ግንኙነት ነው። ላለፉት 1600 ዓመታት ያህል ቤተ ክርስቲያኒቱና ቤተ መንግሥቱ ሊነጣጠሉ እስከማይችሉ በሚመስል መንገድ አንድ ላይ ነበሩ። ይህ ሊስተባበል የማይችል ሐቅ ነው፤ በረጅም ዘመን ታሪኳ ሳትከፋፈልና ወንጌልና “በመስበክ” መቆየትዋ እየደነቀን፣ ለብዙዎቻችን እግዚአብሔርን ለማክበርም፤ ብሎም ብዙ ዕድፏን እያየን ደግሞ አንገት ለመድፋት፤ ለመተከዝ የተገደድንበት ብዙ ጊዜም አለ!

Tuesday, 25 July 2023

ከእሳት የሚያድን፤ በእሳት የሚጠብቅም አምላክ አለን!

 Please read in PDf

እሳት በመጽሐፍ ቅዱስ በብዙ ዓይነት መንገድ ተገልጦአል። ለኹላችንም ግልጥ የኾነው እሳት፣ ሰዎች ለመሥዋዕት አገልግሎት (ዘሌ. 6፥13፤ 1ነገ. 18፥38፤ 2ዜና. 7፥1-3)፣ ለምግብ ማብሰያ (ዮሐ. 21፥9)፣ ለብረት ማቅለጫና (ዘጸ. 32፥24) ለሌሎችም አገልግሎት የሚውል ነው። ይህን እሳት ዓላውያን ነገሥታት አንዳንድ ጊዜ በእነርሱ ላይ ለተነሣሱባቸው ሰዎች፣ የፍርድ መቀጣጫ አድርገው ይጠቀማሉ። ንጉሥ ናቡከደነጾር፣ ለእርሱ ምስል ወይም ጣዖት አልሰግድም ያሉትን ሦስቱን ወጣቶች፣ “… ያስሩ ዘንድ፥ ወደሚነድድም ወደ እቶን እሳት ይጥሉአቸው ዘንድ በሠራዊቱ ውስጥ ከነበሩት ኃያላን አዘዘ። (ዳን. 3፥20)።

ነገር ግን ሦስቱን ወጣቶች የእስራኤል አምላክ ያህዌ ኤሎሂም ታደጋቸው፤ አዳናቸውም፤ ከእስራኤል አምላክ ከቅዱሱ እግዚአብሔርም በቀር ሌላ የሚያድን አምላክ እንደሌለ፣ ያ ዓላዊ ንጉሥ እንዲህ ሲል ምስክርነቱን ሰጠ፤ እኔም እንደዚህ የሚያድን ሌላ አምላክ የለም (ዳን. 3፥29)፤ በእርግጥም ከእሳት የሚያድን ከእግዚአብሔር በቀር ሌላ እንደሌለና በእሳትም ስለሚያከናውናቸው ተግባራት ቅዱሳት መጻሕፍት በምልአት ይመሰክራሉ፤



Thursday, 20 July 2023

የ“አነቃቂዎቹ” ድንዛዜ!

Please read in PDF

ዶክተር ወዳጄነህ መሐረነ “አነቃቂ” ንግግር ያቀርባሉ ከሚባሉ ሰዎች መካከል አንዱ ነው። በአነቃቂዎች ዙሪያ በተደጋጋሚ ለመጻፍ ዐስብና ብዙዎች መልስ በስላቅ፣ በቅኔ፣ በድራማ፣ በ“አሽሙር”፣ በስዕላዊ መንገድ፣ በወግ … መልስ ስለ ሰጡበት ብዙም መናገር አልፈለግኹም። በእርግጥ “አነቃቂ” እንደ ኾኑ የሚያስቡ አካላት፣ እጅግ በሚያደንቅ መልኩ የሕይወት ምሳሌነት የሌላቸው (ኹሉም በሚያስብል መልክ ትዳራቸው በፍቺ የተጠናቀቀ፣ ጾታዊ ግንኙነታቸው አኹንም እንኳ ጤናማ ያልኾነ)፣ ነገረ መለኮታዊ ዕሳቤያቸው ከመጽሐፍ ቅዱስ የማይገጥም፣ ከነባራዊው እውነትና ከማኅበረ ሰቡ መልካም እሴቶች ጋር ፈጽሞ የማይጣጣም፣ ግለኝነትን የሚያበረታታና መንፈሳዊና ማኅበረ ሰባዊ አንድነትን የሚንድ … አመለካከቶችን በውስጡ ያጨቀ ነው።

Sunday, 16 July 2023

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፳፬)

 Please read in PDF

ለባለፉት ጥቂት ወራት ያረጋል አበጋዝ የተባለ ሰው በጻፈውና “መድሎተ ጽድቅ” በተባለው መጽሐፉ ላይ፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምላሾችን እየሰጠን መኾናችን ይታወሳል፤ ዛሬም የዚያን ተከታዩን ክፍል እናቀርባለን። በባለፉት ጊዜያት፣ የ“መድሎተ ጽድቅ” ጸሐፊ፣ የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣን በተደጋጋሚ የሚቃወምበትንና የሚጥስበትን መንገድ እያሳየን መቆየታችን ይታወሳል። አንዳንድ ቦታዎች ላይ የመጽሐፍ ቅዱስን እውነት ተቀባይ ቢመስልም፣ ነገር ግን በሌላ ትምህርት ደግሞ ያንኑ የተቀበለውን እውነት መልሶ ሲክድና በሌላ ትምህርት ሲቃወም እንመለከተዋለን፤ ለምሳሌም፦