ይህን ቃል
የተናገረው ናዛዜ ኅዙናን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ይህንም ቃል የተናገረው ለተወደዱ ደቀ መዛሙርቱ ነው፤
ጊዜውም ደግሞ እርሱ በሥጋ ሞቱ በአይሁድ እጅ ከተገደለ በኋላና በመቃብር ተቀብሮ፣ ደቀ መዛሙርት ኹላቸውም በፍርሃት ቆፈን
ውስጥ፣ “በመሸ
ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ተሰብስበው በነበሩበት፥ አይሁድን ስለ ፈሩ ደጆቹ ተዘግተው ሳሉ፥ ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆሞ፦ ሰላም
ለእናንተ ይሁን አላቸው።” (ዮሐ. 20፥19)።
Friday, 10 February 2023
“ሰላም ለኹላችሁ ይኹን”
Sunday, 5 February 2023
ለዮናስ ነነዌ፤ ለዮናታን አክሊሉ ኦርቶዶክስ፣ ግድ አይደሉም!
እግዚአብሔር፣ ታላቅ ኀጢአት ሠርታ ስለ ነበረችው ነነዌ ሲናገር እንዲህ ይላል፣ “እኔስ ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ ከመቶ ሀያ ሺህ የሚበልጡ ሰዎችና ብዙ እንስሶች ላሉባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ አላዝንምን?” (ዮና. 4፥11)። ዮናስ ምንም እንኳ የእግዚአብሔር ነቢይ የነበረ ቢኾንም፣ ለነነዌ ግን እንጥፍጣፊ ርኀራኄና ሃዘኔታ አለማሳየቱ እጅግ አስደናቂ ነገር ነው። ነቢይነት ሰዎች ወደ እግዚአብሔር እንዲመለሱ በግልጥ የእግዚአብሔርን ዐሳብና ፈቃድ የመናገርን ያህል፣ ስለ ኀጢአት ደግሞ ሲገስጹና ሲቈጡ የእግዚአብሔርን የርኅራኄ ልብ ሳይጥሉና ፍጹም እየሳሱ መኾን ነበረበት።
Friday, 27 January 2023
የአዳዲሶቹ ጳጳሳት ሹመት ስጋት፣ ተስፋዬና ትዝብቴ
ጌታ እግዚአብሔር
በሉዓላዊ አምላክነቱ፣ ክፉውን ነገር ኹሉ ለክብሩ ሊጠቀምበት፣ ወደ በጎ እንደሚያመጣው እናምናለን፤ ኀጢአት እንኳ ከእግዚአብሔር
የሉዓላዊነት ወሰን አልፎ አያውቅም፤ እናም በምድራችን ላይ የምንሰማውን መለያየትና ጥቅመኝነትን ጌታ እግዚአብሔር አጥፍቶ፣
ለሕዝባችን መታነጽና ለክብሩ ታላቅነት እንዲሠራ ከኹሉ በፊት አስቀድመን እንማልዳለን።
አዎን! እግዚአብሔር የፈርዖንን ልበ ደንዳናነት፣ ለሕዝቡ ጥበቃና ትድግና እንደ ተጠቀመበት መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። እግዚአብሔር ሉዓላዊ ነው ስንል፣ በመላለሙ ላይ መጋቢና ሠራዒ፤ አስተዳዳሪና ጌታ ነው እያልን ነው፤ ስለዚህ የምድራችን ነገር የሚገደውና የሚያስብልን ተንከባካቢና ጻድቅ ጌታ አለን ማለታችንም ነው!
Sunday, 22 January 2023
“ጳጳሳቱ”ም እንደ “ጐበዝ አለቃ”
በኢትዮጵያ ፖለቲካ
ታሪክ፣ ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘመናት ለቍጥር በሚታክቱ የጐበዝ አለቆች ሥር ወድቃ ታውቃለች፤ እኒህ የጐበዝ አለቆች “ለሕዝባቸው”
ዘለላ ርኅራኄ የላቸውም፤ ሕዝባቸውን ቆራርሰው ከማስጨነቅ፤ የራሳቸውን ልድልድና ምቹ የዙፋን ሠረገላ ከማመቻቸት የዘለለ፣
ሕዝቡን ሲፈይዱ አልታዩም። እንዲያውም “የሰኞ ገዳይ”፣ “የማክሰኞ መጋቢ” ተባብለው በሳምንቱ ቀናት ላይ ተሿሹመው አስጨናቂ
አስገባሪዎች እንደ ነበሩ ዛሬም ድረስ የምናስተውለው እውነታ ነው።
Wednesday, 18 January 2023
የመንፈስ ቅዱስ እንደ ርግብ መውረድ
በጥምቀት ወራት ከሚነሡት ዐሳቦች መካከል
አንዱ፣ “ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ
በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤” (ማቴ. 3፥16) የሚለው ቃል ይታወሳል። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲጠመቅ፣ መንፈስ ቅዱስ እንደ
ርግብ በጌታችን ላይ ወረደ።
Tuesday, 17 January 2023
መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፳፫)
“በመድሎተ ጽድቅ” መጽሐፍ ውስጥ፣ የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣን በተመለከተ ጐልተው
የሚታዩትን ስህተቶች በባለፈው ክፍል ከጠቀስናቸው ስህተቶች ባሻገር የሚከተሉትም ይካተቱበታል።
1.2.
የተባለውን በትርጉም በመቃወም፦
የመድሎተ
ጽድቅ ጸሐፊ፣ መዳን በክርስቶስ ብቻ እንዳልኾነና በመዳን ውስጥ እኛም ድርሻ እንዳለን ለማሳየት ከተጠቀመበት ጥቅስ አንዱ እንዲህ
የሚል ነው፤
“ኦርቶዶ ክሳውያን አባቶቻችን የጸጋው ሥጦታ ነጻ(እንዲሁ) የሚሰጥ መኾኑን በአንድ በኩል ፣ የሰውን ነጻ ፈቃድ (ነጻነት)
ደግሞ በሌላ በኩል አስተባብረው በመያዝ ለሰው መዳን የኹለቱ መስተጋብር አስፈላጊ መኾኑን በአጽንዖት ያስተምራሉ። ይህም በቅዱስ
ጳውሎስ ከእርሱ ጋር አብረን የምንሠራ ነንና።” ተብሎ የተገለጸው
ነው(1ቆሮ. 3፥9)”
Friday, 6 January 2023
ጌታዬ ኢየሱስ ለእኔ የተወለደባቸው ምክንያቶች
በምድራችን ላይ
ሲሰሙ ከሚወደዱ ታላላቅ ምሥራቾች ኹሉ፣ የሚልቀውና አቻ የሌለው ምሥራች፣ የጌታችን ኢየሱስ መወለድን የሚያህል ሌላ ምሥራች
የለም! መልአኩ እንዲህ አለ፣ “እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤
ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።”
(ሉቃ. 2፥10-11)፤ ለሰው ኹሉ የሚበቃና ሰውን ኹሉ በእኩል ደስ ማሰኘት የሚችል ምሥራች ከክርስቶስ በቀር አለመኖሩ እንዴት
ይደንቃል!
Saturday, 31 December 2022
“የእግዚአብሔር መንፈስ ያለባቸው መጻሕፍት ሁሉ - ኒዎኔወስቶስ” (2ጢሞ. 3፥16)
ቅዱስ ጳውሎስ ኹለተኛ ጢሞቴዎስን ሲጽፍ፣ የኑዛዜ ያህል በሞቱ ዋዜማ ነው (4፥6)፤ የሚጽፍለት ደግሞ
“በመንፈስ ለወለደው ልጁ” (1፥2) ቅዱስ ጢሞቴዎስ ነው፤ ለዚህ ተወዳጅ ባላደራ አገልጋይ፣ የቅዱሳት መጻሕፍትን እስትንፋሰ
እግዚአብሔርነት በግልጥ ይጽፍለታል። ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ክፍል፣ መጽሐፍ ቅዱስን፣ “ቅዱሳት መጻሕፍት” እና የእግዚአብሔር
መንፈስ ያለባቸው መጻሕፍት” በማለት ይጠራቸዋል። “ኒዎኔወስቶስ” የሚለውም የግሪክ ቃል፣ የቅዱሳት መጻሕፍትን የእግዚአብሔር እስትንፋስነት የሚገልጥ ቃል ነው።
Sunday, 25 December 2022
ሄኖክ ኃይሌ(ዲያቆን) ስለ አዋልድ መጻሕፍት ያሳየው ደካማና ጠንካራ ሙግቱ!
ሄኖክ ኃይሌ፣ ስለ ተአምረ ማርያም በጻፈው ኹለተኛ ክፍል ላይ እስካኹን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ
ቤተ ክርስቲያን፣ አዋልድ መጻሕፍትን (ማለትም ትርጓሜያትን፣ ገድላትን፣ ድርሳናትን፣ መልክዐ መልክዕን፣ ተአምራትን፣ ነገራትን፣
ፍካሬያትን) ለማስተካከልና ለማደስ የተቸገረችበትን ምክንያት ሲጠቅስ እንዲህ ይላል፤
“ … ላለፉት ሠላሳ ዓመታት ያሳተሟቸውና በነጻ ያደሏቸው መጻሕፍት … ክርስቶስን ‘ጨርሶ አታውቂም’
የሚሏትን ከሳሾችዋን በማስታገሥ ሥራ ላይ ተጠምዳ እንድትቆይ ግድ ኾኖባት ቆይቶአል።”
Friday, 16 December 2022
ዮናታዊ ቀበሮነት!
በግልጽ ቃል የዮናታን ዓላማ ቅዱስ ወንጌልን መስበክ አይደለም፤ ዓላማው ቅዱስ ወንጌልን መስበክ ቢኾን
ኖሮ፣ “የቃል እምነት እንቅስቃሴ” ከሚባል ነሁላላ ትምህርት አስቀድሞ ራሱን ባረቀና በጠበቀ ነበር። ነገር ግን ይህ የኑፋቄ
ትምህርቱ እንዳይታወቅበት፣ የኦርቶዶክስን ድርሳንና ገድላት በመንቀፍና በመተቸት “ራሱን ወንጌላዊ አድርጎ ለማቅረብ” ብዙዎችን
ያሞኛል፤ ያጃጅላል።
Monday, 12 December 2022
ተሐድሶ እንዴት ይታያል? የመጨረሻ ክፍል
ካለፈው የቀጠለ …
የቤተ ክርስቲያኒቱ ሥርዓታት የዶግማ ማስፈጸሚያ ሥልቶች ናቸው። ለምሳሌ መጠመቅ የግድ ነው፦ ዶግማ ነው፤ የአጠማመቅ ኹኔታ ግን ሥርዓት ነው። ቁርባን ዶግማ ነው፤ ‹እንዴት መቁረብ ይኖርብናል?› በሥርዓት መልስ ያገኛል። በዚህ ዓይነት ከሐዋሪያት ጀምሮ ያሉ አባቶች ከኅብረተ ሰቡ የአኗኗር ሁኔታ ጋር የሚስማሙና ለጽድቅ ሥራ የሚያበቁ የእምነት መተግበሪያ ስልቶችን ነድፈዋል፤ እንደ ኹኔታውና እንደ ኅብረተ ሰቡ እያዩም ሊያስተካክሉት ይችላሉ።
Sunday, 11 December 2022
ተሐድሶ እንዴት ይታያል? ክፍል ፩
ከረጅም ጊዜያት ጀምሮ የተሐድሶ ጉዳይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አነታራኪ ኾኖአል። ንትርኩም “ባፍ በመጣፍ” እንደሚባለው ኾኖአል ማለት ይቻላል። ንትርኩና ፍትጊያው አኹንም ድረስ ያለና እንዲያውም፣ በአኹን ወቅት ደግሞ በኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ “ጸረ ተሐድሶ የተባሉ ኮሚቴዎች” የተቋቋሙበትና ከፊት ይልቅ በጽኑ ለመቃወም ቅስቀሳ እንዳለ ጸሐፊው ያስተውላል። ንትርኩና ጭቅጭቁ ደግሞ፣ ቀለል ከሚለውና ለመመለስ ግን ከሚቸግረው፣ “ተሐድሶ የሚባለው እንቅስቃሴ አለ ወይስ የለም?” ከማለት ይጀምራል። እኔም ከዚሁ፣ “እውን የተባለው የተሐድሶ እንቅስቃሴ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ እየተካሔደ ነው ወይስ የለም?” ብዬ በመጠየቅ ልነሳ ፈለግኹ።
Saturday, 3 December 2022
የዕብራውያን መልእክት ዓላማና የእኛ ዘመን መመሳሰል!
ኢየሱስ
ከይሁዲነት ይልቃል!
ኢየሱስ
ከኦሮሞነትና ከአማራነት ከሌሎችም ይልቃል!
ኹሉም የመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍት የተጻፉበት የየራሳቸው ዓላማ አላቸው፤ የመጻሕፍቱ ዋነኛ ዓላማ ማጠንጠኛው ደግሞ፣ የእግዚአብሔር መንግሥትን ማዕከል ያደረጉ ናቸው፤ ከዚህም የተነሣ ዓላማቸው የሚበልጠውንና የሚልቀውን የእግዚአብሔርን ዐሳብና ፈቃድ ማሳየት ነው። ከዚህ አንጻር የዕብራውያን መልእክትን ስንመለከት፣ ኹለት ዋና ዋና ዓላማዎችን ማውጣትና መናገር እንችላለን።
የመንፈስ ቅዱስ ጸጋዎች ቀርተዋል ለማለት አንሻፍፈው የሚተረጕሟቸው ጥቅሶች
“በአሁኑ ዘመንም የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴ በሚታይበት ቦታ ኹሉ አንዳንዶች ያፌዛሉ፤ ሌሎች ደግሞ እውነተኛ ምልክት
እያዩ “ዐይኔን ግንባር ያድርገው” በማለት ለአኹኑ ዘመን አይደለም የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች በሐዋርያት ዘመን አክትሟል ሲሉ ሌሎች
ደግሞ “ተጠንቀቁ” በማለት በድፍኑ መሸሽን ይመርጣሉ።”[1]
ኹሉም የስሕተት አስተማሪዎች የመጽሐፍ ቅዱስን ክፍሎች ለትምህርታቸው
ዋቢነት ከዐውዱ ውጭ ቦጭቀው በማውጣትና በመጥቀስ ዘወትር ይታወቃሉ። የቅዱሳት መጻሕፍትን ሐሳብ ለገዛ ትምህርታቸው በማጣመም ይታወቃሉ፤
ግልጡን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በማጣመም ወይም አወሳስቦ በመተርጐም የሚያኽላቸው የለም፤ ቅዱስ ጴጥሮስ “በእነዚያ ዘንድ ለማስተዋል
የሚያስቸግር ነገር አለ፥ ያልተማሩትና የማይጸኑትም ሰዎች ሌሎችን መጻሕፍት እንደሚያጣምሙ እነዚህን ደግሞ ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ”
እንዲል (2ጴጥ. 3፥16)።
Monday, 21 November 2022
ተሐድሶን ለማጥፋት መወሰድ ያለባቸው ርምጃዎች! (የመጨረሻ ክፍል)
2. የተሐድሶን ጥያቄዎች መቀበል
የተሐድሶን ጥያቄዎች በደፈናው ከመቃወምና አገልጋዮችን ከማውገዝ ይልቅ፣
በቅንነትና በእግዚአብሔር ቃል መሰረት መዝኖ ጥያቄዎችን መቀበል ተሐድሶን ለማጥፋት የመጀመሪያ ርምጃ ነው። ይህም ርምጃ
ምናልባት በአገልጋዮች እውቀትና ልምድ ማነስ ምክንያት ሊከሰት የሚችለውን ከተሐድሶ ዓላማ ጋር የማይሄድ ችግር ለማስቀረትና ሙሉ
ለሙሉ በተሻለ አቅም ተሐድሶን ለመምራት ያስችላል።
ተሐድሶን አልፈልገውም ተብሎ አይካድም፤ ምክንያቱም ተሐድሶ በራሱ መንገድ የእግዚአብሔር ቃል በተነገረበት፣ የእግዚአብሔር ስም በተጠራበት እንዲሁም የእግዚአብሔር መንፈስ በሚሠራበት ቦታ ኹሉ የሚከሠት እንቅስቃሴ እንጂ ልናስቀረው የምንችለው ጉዳይ አይደለምና።














