ኹለት ልብ የለኝም
ኹለት ኑሮ አላውቅም
ኹለት ቤት የለኝም
(የታማኝ ትዳር ውብ ምሳሌ)
መጽሐፍ ቅዱስ፣ እጅግ
አስደናቂ ስለ ኾኑ ሴቶች ካስቀመጠልን ሕያው ምስክር አንዷ አቢግያ ናት፤ እንዲህም የተመሰከረላት፣ “የሴቲቱም
አእምሮ ታላቅ፥ መልክዋም የተዋበ ነበረ፤” (1ሳሙ. 25፥3)። በተቃራኒው አቢግያ የስሙ ትርጓሜ “ጅል” ተብሎ ለሚጠራው
ለናባል ሚስቱ ነበረች፤ እርሱ በምግባሩ “ባለጌ፥ ግብሩም ክፉ ነበረ፤ ከካሌብም ወገን የኾነና
… ምናምንቴና ባለጠጋም ነበረ” (ቊ. 3፡ 25)። ሰውየው ባለጌ፣ ግብረ ክፉ፣ ካሌብ የስሙ ትርጉም “ውሻ” እንደ ኾነ፣ የውሻ
ጠባይ ያለው ሰው ነበረ፤ ከሚስቱ ፍጹም ተቃራኒ ሰው!
ካለፈው የቀጠለ …
ባለፉት ጊዜያት የ“መድሎተ
ጽድቅ” መጽሐፍን በቀጥታ በመጽሐፍ ቅዱስ ከመመዘናችን በፊት፣ በመጽሐፉ ውስጥ ከቅዱሳት መጻሕፍት ዐሳብ ውጭ በኾነ መንገድ እንደ
ገና ተተርጕመው የቀረቡትን ቃላት መመልከት መጀመራችን ይታወሳል። ቃላቱን በተመለከተ ዛሬም ቀጣዩን ክፍል የምናቀርብ ይኾናል። መልካም
ንባብ።
· መዳን፦ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥና በአጭር ቃል ስለ መዳን ሲናገር እንዲህ ይላል፣ “በእርሱ[በክርስቶስ] የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።” (ዮሐ. 3፥16)። በመጽሐፍ ቅዱስ መዳን የሚለው ዐሳብ፣ ልክ በዚህ ክፍል እንደ ተጠቀሰው የዘላለም ሕይወት፣ አዲስ ልደት (ቲቶ 3፥5)፣ አዲሱን ሰው መልበስ (ቈላ. 3፥10)፣ አለመጥፋት (ዮሐ. 3፥16፤ 2ጢሞ. 2፥11)፣ ልጅነት (ሮሜ 8፥13)፣ ዳግመኛ መወለድ (ዮሐ. 1፥12-13፤ 3፥3-8) በሚሉ ተካካይ ዐሳቦች ገልጦት እንመለከታለን።
በእግዚአብሔር ቸርነትና የተትረፈረፈ
ምሕረት፣ ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት በብሎግ ወይም በጡመራ መድረክ አገልግሎት አገልግያለሁ፤ በእነዚህ ዓመታት ከእግዚአብሔር የሰማኋቸውን፣
የተቀበልኳቸውን፣ ቅዱስ ቃሉን ሳነብብና ሳጠና መንፈስ ቅዱስ የገለጠልኝን፣ በኢትዮጵያ በተለያዩ ቦታዎች የደረሱትን እጅግ አሳዛኝ
ሰቆቃዎችንና ከፍ ያሉ በደሎችን በአካል በስፍራው ተገኝቼ በመመልከት እግዚአብሔር ምን ይሰማው ይኾን? ብዬ ሙሾ አውርጄአለሁ።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ
ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የዓቢይ ጾም የመጀመሪያው ሳምንት ስያሜ “ዘወረደ” ወይም “ጾመ ሕርቃል” ይባላል። የመጀመሪያውን ሳምንት
“ዘወረደ” የሚለውን ስያሜ ያገኘው በባለዜማው ያሬድ ሲኾን፣ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ከሰማያት መውረድና የሰዎችን ልጆች ለማዳን
ያደረገውን የውርደት መንገድ በማሰብ፣ ከቅዱሳት መጻሕፍት ንባባት እየተነበበ አምልኮ የሚቀርብበትም ሳምንት ነው። ይኸው ሳምንት
ከዚህ ከጌታችን ባሕርይ ተቃራኒ በኾነ መንገድ “ጾመ ሕርቃል” ተብሎም ይጠራል።
የጾመ ሕርቃል አጭር ጥንተ ታሪክ[1]
መቼም የሐሰት መምህራንን
ጠባይ መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር እንዲህ ይላል፣ “ክፉዎች
ሰዎችና አታላዮች፥ እያሳቱና እየሳቱ፥ በክፋት እየባሱ ይሄዳሉ” (2ጢሞ. 3፥13)። አንድ የስህተት አስተማሪ ፈጥኖ በቅዱስ ፍርሃትና የቅዱሳት መጻሕፍትን
ሥልጣን በማክበር በመታዘዝ ካልተመለሰ፣ እየባሰ፣ እየከፋ፣ ኀጢአቱን እየጨመረ፣ አሳሳችነቱን ይበልጥ እየገፋበት ይሄዳል።
ዘጠነኛ ክፍል እንግሊዘኛ ያስተምሩን አስተማሪያችን ይኅደጐ ይባላሉ፣ ማስተማር
ከመጀመራቸው በፊት ጥቊር ሰሌዳውን በሚገባ ደጋግመው ያጸዱት ነበር፤ አንድ ቀን አንዱ ተማሪ፣ “ቲቸር ለምን እንዲህ ውልውል አድርገው
በሚገባ ያጸዱታል?” ብሎ ጠየቃቸው፤ እነርሱም፣ “በሚገባ ባልታጠበ ትሪ ምግብ ትበላለህ?” ብለው ጥያቄውን በጥያቄ መለሱለት። እኔም
ዛሬ ሳስተምር፣ እንደ ቀደመው አስተማሪዬ በሚገባ መወልወልን ልማዴ አድርጌ አስቀርቼዋለሁ። ወደ ክርስትና ስመጣ የእኒህ አስተማሪ
“መርህ” በዋዛ የሚታለፍ አይደለም።
ጥንተ ታሪክ
ሊመጣ ካለው ቊጣና ፍርድ ታመልጥ ዘንድ፣ የንስሐ ዕድልን ሊሰጥ እግዚአብሔር
የአማቴ ልጅ ዮናስን ወደ ነነዌ ላከ። ነገር ግን ነቢዩ ዮናስ እግዚአብሔር ላዘዘው ምላሹ አለመታዘዝና ወደ ራሱ ፈቃድ አዘንብሎ
ከእግዚአብሔር ፈቃድ ሸሸ። እግዚአብሔር ግን ሉዓላዊና ኹሉን ሲያደርግ የሚሳነው የሌለ ነውና ዮናስን ወደ ነነዌ በራሱ ማጓጓዣ [በተአምራዊ
መንገድ] በዓሳ አንበሪ ሆድ ጭኖ ነነዌ አደረሰው።
ራቪ ዘካርያስ፣ “የገዛ ሚኒስትሪያቸው” ያረጋገጠባቸው አስቀያሚው የዝሙት ገመና ብዙ ነገሮችን እንዳብሰለስል አድርጎኛል። በርግጥ ከደካማው ሥጋ ለባሽ ይልቅ፣ ቅዱስ ቃሉ የማይለወጥና ብርቱ አስተማሪያችን፣ የሚረባንንና የሚጠቅመንን የሚነግረን ኹነኛ መምህራችን ነበረ፤ እንዳለመታደል በትክክል ከመስማትና ከመታዘዝ ቸል አልን እንጂ። አዎን መጽሐፍ ቅዱስ “የብርቱዎችን” ድካም ያራቆተው፣ እንማርበትና እንታነጽበት ዘንድ እንጂ እንገበዝበት ዘንድ አይደለም።
ካለፈው የቀጠለ …
·
እግዚአብሔርን መምሰል፦
“በርካታ የምዕራብ
ክርስቲያኖች የኦርቶዶክስን የቲኦሲስ ወይም እግዚአብሔርን የመምሰል ሥነ ሐሳብ በትክክል ሊረዱት አልቻሉም። በተለይም ‘ሰው አምላክ
ይኾን ዘንድ አምላክ ሰው ኾነ’ የተሰኘውን የቅዱስ አትናቴዎስን ጥቅስ ሲያነቡ፣ ይህ የምሥራቃዊ ሂንዱይዝም ወይም የፓንቴይዝም ተጽዕኖ
ነው በማለት ያስባሉ።”[1]
“በቅድስና እግዚአብሔርን
በመምሰል የማደግ ሂደትም ከእግዚአብሔር ቅድስና የመሳተፍ ሱታፌያዊ ሂደት ነው። … ሐዋርያው፣ ‘ … ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥
በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን።’ ያለው የባሕርዩ መገለጫና መታወቂያ የኾኑትን ነገሮች
- ኃይላተ እግዚአብሔር ቅድስና፣ ቸርነት፣ ደግነት፣ ጥበብ፣ እውነተኛነት፣ ገዢነት … የመሳሰሉትን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ የተሰጠን
በመኾኑ ነው። ይህም ከፓንቴይዝም እርሾ የጸዳ መጽሐፍ ቅዱሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርት ነው።”[2]
መግቢያ
በብዙዎች ዘንድ ከምንከሰስበት ነገር አንዱ፣ “ስለ ማርያም አትሰብኩም፤ ስለ ቅዱሳንም አትመሰክሩም” የሚል ክስ ነው። ይህን የሚሉ አካላት እያወቁም ይኹን በጽንፈኝነት ከመጽሐፍ ቅዱስ ተቃራኒ በመኾን ዘመናቸውን ስለ ማርያምና ስለ ቅዱሳን “በመስበክ” ይከስራሉ። ከዚህም የተነሣ አያሌዎች ማርያምን በመስበክ የታወቁ ናቸው። ከሰሞኑ እንኳ ካየነው የዘበነ ለማን ዓይን ያወጣ ግብዝነት ማንሳት እንችላለን። ይህን ሳሰላስል የመጣልኝ አንድ አስቂ ታሪክ አለ። መልአኩ ሚካኤል አንድ ክንፉ ያዘቀዘቀበት ምክንያትና የማርያም ከፍጥረተ ዓለሙ በፊት መታየት።
መግቢያ
በመጽሐፍ ቅዱስ ዋና
ዋና ከሚባሉት ትምህርቶችና አማኞች ሊጠመቁት ከሚገባው ጥምቀት አንዱ፣ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ነው። የብዙዎች ትኵረትና መሻት ያለው
የውኃ ጥምቀትና በየዓመቱ ከጥምቀት በዓል ጋር ተያይዞ የሚከበረውን የከተራ በዓልን እንጂ ስለ መንፈስ ቅዱስ ጥምቀት እምብዛም ግንዛቤው
ያላቸው አይመስልም። ነገር ግን አስገዳጅ ከኾኑ መንፈሳዊ እውነቶች አንዱ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ነው፤ በመንፈስ ቅዱስ ያልተጠመቀ
እርሱ እውነተኛ አማኝ ወይም መንፈሳዊ አይደለም።
ካለፈው የቀጠለ …
·
የእግዚአብሔር ቊጣ፦
መጽሐፍ ቅዱስ፣ ኀጢአት የእግዚአብሔርን ቊጣ እንደሚያነሣሣ በግልጥ ይናገራል፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ባሕርይውና ፈቃዱ ቅዱስና ጻድቅ ነውና፣ በኀጢአት ፈጽሞ አይደሰትም። በሌላ ንግግር ኀጢአትን ፈጽሞ ይጠየፋል፣ ይጠላልም፤ በኀጢአት ከቶም ደስ አይሰኝም ማለታችን ነው። አደራረጉ ፍጹም ቅዱስና ንጹሕ ነው። ስለዚህም “በቍጣውና በመዓቱ ኀጢአተኞችን ይገለባብጣቸዋል፤ ኪዳኑን የሚተዉትንም ይነቅላቸዋል፤ ” (ዘዳ. 29፥23-28)። ቅዱሱ እግዚአብሔር፣ ያለ ተጨባጭ ምክንያት እንደ ሰው በንዴትና በብስጭት የሚቈጣ አይደለም፤ ቊጣው ወዲያው የሚነሣ ደግሞም ቶሎ የሚበርድም አይደለም። በተለይ ኀጢአተኞችን ለኀጢአታቸው በመተው ቊጣው ይገለጣል፤ (ሮሜ 1፥24)።
ዛሬ ላይ በምንም ዓይነት ሚዛን፣ አጼ ኃይለ ሥላሴን እንዲያ መዋረዳቸውን፣ 60ዎቹ ሚኒስትሮቻቸው ደግሞ በአንድ ጉድጓድ ውስጥ በጅምላ ተገድለው መቀበራቸውን የሚደግፍ ሰብዓዊና ጤነኛ ሰው ይኖራል ብዬ አልገምትም። ይህን የማይደግፈው አጼው አልበደሉም፤ ሚኒስትሮቻቸውም ንዑዳን፤ ቅዱሳን ናቸው ብሎ እንዳይደለ፤ ነገር ግን አገር ለመሩ፣ ጥቂት ውለታ ለዋሉ ምንም ያህል ክፉ ቢሠሩ ብድራታቸው ግድያ፤ በጅምላ መረሸን፣ መዋረድና መንገላታት እንዳልኾነ ዕዝነ ልቡናው ያስባል፤ ያሰላስላል ብዬ እንጂ።