Saturday, 24 October 2020

ከፖፑ ባሻገር፣ የእኛስ ነገር?

 Please read in PDF

ግብረ ሰዶማዊነት በኢትዮጵያ ስላለበት ኹኔታ ፍርሃት አለኝ!

ከጥቂት ዓመታት በፊት በእጅ ስልኬ ላይ አንዲት እህት ደወለች፤ አነሳሁት። ሰቅጣጭ ልቅሶና መራራርነት ከድምጿ ይነበባል። እናም ሕይወቷን መጥላቷን፣ ራሷንም ልታጠፋ መዘጋጀቷንና የመጨረሻ የመፍትሔ ዕድሏን ለመሞከር መደወሏን ነገረችኝ። ከብዙ ተማህጽኖና ምክር በኋላ ላገኛት ወስኜ አገኘኋት። ሳገኛት መርዝና ገመድ አዘጋጅታ ራስዋን ለማጥፋት ወስና የተዘጋጀች መኾኑን አስተዋልኩ። በጌታ ብርታት ክፉ ተግባርዋን እንድትተው ካደረግሁ በኋላ ታሪኳን መስማት ጀመርኩ።

Thursday, 22 October 2020

ፖፑን ምን ነካቸው?

 Please read in PDF

መግቢያ

የሮሙ ፖፕ ፍራንሲስ ያለፈው ማክሰኞ ግብረ ሰዶማውያን በአንድነት እንዲኖሩ መፍቀዳቸውን፣ ይህም የእግዚአብሔር ፈቃድ መኾኑንና እኛም ዕውቅና ልንሰጣቸው እንደሚገባቸው መናገራቸውን እየሰቀጠጠኝ ተመልክቻለሁ። ምክንያታቸውንም ሲያቀርቡ፣ “እነሱ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው። ግብረ ሰዶማውን የቤተሰቡ አባል የመኾን መብት አላቸው። … እኛ መፍጠር ለብን የሲቪል ማኅበራት ሕግ ነው። በዚያ መንገድ በሕጋዊነት ተሸፍነዋል። ለዚህም ቆሜአለሁ።”  በማለት ተናግረዋል።[1]

Tuesday, 20 October 2020

ስላንተ ልጣላት

Please read in PDF

አልወድህም አንተን አልወድህም የምር
ከአንደበት አያልፍም ላንተ ያለኝ ፍቅር

Monday, 12 October 2020

የልጁን መልክ መምሰል (ክፍል ፬ና መጨረሻ)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ…

ይህን ማወቅ ለምን አስፈለገ?

እግዚአብሔር ሃይማኖታዊ ዝንባሌና መልኩ ብቻ እንዲኖረን አይወድም። “ሙሉ ሰው ወደ መሆን፥ የክርስቶስም ሙላቱ ወደሚሆን ወደ ሙላቱ ልክ እስክንደርስ ድረስ” ለማደግ፥ “ሁላችን የእግዚአብሔርን ልጅ በማመንና በማወቅ ወደሚገኝ አንድነት መምጣት (ኤፌ. 4፥13)፤ ስለ እውነት ስለ እግዚአብሔር ልጅ ዕውቀት ሊኖረን ይገባል።

Wednesday, 7 October 2020

የልጁን መልክ መምሰል (ክፍል ፫)

Please read in PDF

እንዲህ ነበርን!

ካለፈው የቀጠለ...

5. በአሳባችን ጠላቶች ነበርን፦ ኹላችን በእግዚአብሔር ፊት፣ “… ክፉ ሥራንም በማድረግ በአሳባችን ጠላቶች ነበርን” (ቈላ.1፥21-22)፡፡ እጅግ ክፉዎች ከመኾናችን የተነሣ በእእምሮአችንና በልባችን ለራሳችን የምናዳላ ራስ ወዳዶች ነበርን፡፡ በምድር ላይ አንድም መልካም ሰው መገኘት እስከማይችል ድረስ ኹላችንም ለእግዚአብሔር ጠላቶች ነበርን፡፡

Wednesday, 30 September 2020

እሬቻ አምልኮ አይደለምን?!

 please read in PDF

መግቢያ

   ስለ እሬቻ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከምንሰማቸው ልዝብ አሳቦች አንዱ፣ “የኦሮሞ ባህልን የምናንጸባርቀበት ብቻ እንጂ አንዳችም አምልኮአዊ መልክ የለውም” የሚለው ግንባር ቀደሙን ስፍራ ይይዛል። ይህን ለማለት ያስደፈረው እውነታ ደግሞ በክርስትና ጥላ የተጠለሉ አያሌ ኦርቶዶክሳውያንና የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት “አማኞች” እና ስለ እሬቻ ዘብ የቆሙ ሰዎች የሚያቀርቡት የተለሳለሰ ዐሳብ ነው። እሬቻን የሚያከብሩት ኦርቶዶክሳውያንና የወንጌላውን አብያተ ክርስቲያናት አማኞች፣ አምልኮአዊ መልክ እንዳለው ስለ ገባቸው ወይም ስለ ተጠራጠሩ፤ በሌላ መልኩ ደግሞ “ባህላችንን እንወዳለን” የሚል አባባይ ምክንያት በመጥቀስ ለማስረዳት ሲንገታገቱ አስተውያለሁ።



Saturday, 26 September 2020

መስቀሉን የማያውቅ መስቀል

 Please read in PDF

መግቢያ

  በአገራችን በኢትዮጲያ ከሚከበሩት ሃይማኖታዊ በዓላት መካከል አንዱ ከደመራ ጋር ተያይዞ የሚከበረው በዓል  ነው፤ በዓሉ፣ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት እንጨቱ መስቀል፣ ለዓመታት ከተቀበረበት ቦታ መውጣቱን በማሰብ የሚከበር በዓል ነው። በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳይኾን፣ ይህ የመስቀል በዓል በአያሌ የአገራችን ሕዝብ ባህሎች ውስጥ የተለያየ መልክና ቅርጽ ይዞ ሲከበር እንመለከታለን። ሃይማኖታዊው ትውፊት መስቀሉ ከተቀበረበት መውጣቱን በማሰብ ሲያከብር፣ አያሌ ባህሎች ደግሞ ከዘመን መለወጫ ጋር በማያያዝ በዓሉን ያከብሩታል።

Wednesday, 23 September 2020

የአሸናፊ ገብረ ማርያም(ቀሲስ) “ጐስአ ልብየ ቃለ ሰናየ” ማርያም ናትን?

 Please read in PDF

መግቢያ

  አሸናፊ ገብረ ማርያም(ቀሲስ) ጥቂት የማይባሉ መዝሙሮችን “ሠርቶ”፣ ከሰንበት ትምህርት ቤት ጀምሮ ተጠቅመንባቸዋል፤ ታንጸንባቸዋል፤ አምልከንባቸዋል። ለጌታ የሚሠራቸው መዝሙሮች እጅግ መሳጭና ትኵረትን ቀንብበው የሚይዙና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያላቸው ናቸው። በዚህ ረገድ ከማከብራቸውና ከምወዳቸው ዘማሪዎች መካከል አንዱ ነው።

Saturday, 19 September 2020

የልጁን መልክ መምሰል (ክፍል ፪)

Please read in PDF

እንዲህ ነበርን!

    አዳም “የመታዘዝን ፍሬ” ባለመብላት እንዲታዘዝ ቢነገረውም፣ እርሱ ግን የሰይጣንን ድምጽ ተከትሎ በመሄድና የተከለከለውን ወስዶ ከበላበት ቀን ጀምሮ ክርስቶስ እስኪመጣ ድረስ እርሱና ልጆቹ ሁሉ፣ እግዚአብሔር የተወን እየመሰለን አብዝተን ኃጢአትን ሠራን፤ ጨመርንም። ከዚህም የተነሣ፦

Thursday, 10 September 2020

... ደረስክ የሚባለው...

Please read in PDF

በአሮጌ ሰውነት ቀኑ ቢግተለተል

ዓመት፤ ዓመት ወልዶ ዘመኑ ቢቆለል

Tuesday, 8 September 2020

ያለ ኢየሱስ ስርየት የለም!

 Please read in PDF

  ጳጉሜ 3 ብዙዎች ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የሚላተሙበትን ድርጊት የሚፈጽሙበት ቀን ነው፤ በሌላ ቋንቋ፣ “የእግዚአብሔርን ልጅ የረገጠ ያንንም የተቀደሰበትን የኪዳኑን ደም እንደ ርኵስ ነገር የቆጠረ የጸጋውንም መንፈስ ያክፋፋ፥ እንዴት ይልቅ የሚብስ ቅጣት የሚገባው ይመስላችኋል?” (ዕብ. 10፥29) የሚለውን ቃል በግልጥ የሚቃወሙበት ቀን ነው፤ “በመልአኩ ሩፋኤል” ስም መጠበል ወይም መጠመቅ ከኀጢአት ያነጻል የሚል ከንቱ ልፍለፋ።

Thursday, 3 September 2020

Sunday, 30 August 2020

የልጁን መልክ መምሰል (ክፍል ፩)

Please read in PDF

    “ሁላችን በሃይማኖትና የእግዚአብሔርን ልጅ በማወቅ አንድ እስክንሆን ድረስ በክርስቶስ ፍጻሜ ልክ የአካል መጠን እንዲደርስ ፍጹም ሰው እንሁን” (ኤፌ.4፥13)

መግቢያ

    በዘመናችን ሰዎች ክርስቶስን በትክክል መኾን እንደሚቻላቸው አያሌ የስህተት ትምህርቶችን መስማት ከጀመርን ሰነባብተናል። አንዳንዴ ክርስቶስን የፍጥረቱ አካል በማድረግ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ እኛ ራሱ ክርስቶስን ልንኾን እንደምንችል በአደባባይ ታውጆአል፤ በተለያየ መንገድ ይህን ትምህርት ፊት ለፊት በመቃወም፣ የትምህርቱን ስሑትነትና ከመጽሐፍ ቅዱስ ያልተቀዳ መኾኑን ተናግረናል፤ አስተምረናል። ዛሬም ክርስቶስ የፍጥረት አካል እንዳይደለ፤ ቅዱሳት መጻሕፍት ያስተማሩንን፣ ፍጹም አምላክነቱና ፍጹም ሰውነቱን  ደፍረን እንናገራለን።

Tuesday, 18 August 2020

የመጽሐፍ ቅዱሱ ክርስቶስ - ክብሩና ሞቱ (ሉቃ. 9፥28-36)

  Please read in PDF

  በግርማ መለኮት የተፈራውና ማንም ሊቀርበው የማይችለው ጌታ፣ በክበበ ትስብእት በናዝሬት ከምትኖር ከአንዲት ድኻ ሴት ከማርያም ተወልዶ፣ በተዋረደው ዓለም በውርደት ተመላለሰ። ከመሰቀሉ በፊት ሰውን ሥጋ በመልበሱ ብቻ ተዋረደ። በበረት ከመወለዱ በፊት፣ በናዝሬት መንደር ከአንዲት ሴት ማኅፀን በማደሩ እጅግ፤ እጅግ ዝቅ አለ። ከኀጢአተኞች ጋር በመቈጠሩና ከእነርሱም ጋር በመዋሉ ደግሞ ኢየሱስ፣ ስድባችንን ኹሉ በመሸከም መስቀሉን በመላ ዘመኑ ታገሠ።

Saturday, 15 August 2020

ስለ ማርያም “ከሚሸቅጡ” ተጠበቁ!

Please read in PDF

   መጽሐፍ ቅዱስ የሚናገረውን ብቻ መናገር አስተዋይነት፤ ያልተናገረውን ደግሞ አለመጨመር ፍጹም ታማኝነት ነው። እኛ ሰውን ደስ ለማሰኘት የተናገርነው “እውነት”፣ መጽሐፍ ቅዱስ ደግሞ ያልተናገረው ሐሰት ሊኾን የሚችልበት አንዳች ሚዛን የለም፤ የእውነት እውነተኛው ሚዛን መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ከኾነ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ያልተናገረውና ያላለው ኹሉ ሐሰት፣ እርሱ የተናገረውና በእርሱ ያለው ብቻ እውነት ነው። ሚዛንን ስቶ ሚዛናዊ መኾን ፈጽሞ አይቻልምና።