Saturday, 25 July 2020

ቀናነት እንዳንተው!

Please read in PDF


ደም እንዳሰከረን ደም እንደ ተጣባን
እንደ ንዳድ ወርሶ ቂም እንዳጐበጠን

Sunday, 28 June 2020

የእምነት እንቅስቃሴ አገልጋዮች የክርስቶስን ዘላለማዊ ልጅነት አያምኑም!


(“የእምነት እንቅስቃሴ - የዛሬቱ ቤተ ክርስቲያን ፈተና”፣ ከሚለው መጽሐፍ ገጽ 61-63 የተወሰደ)
3.1.   ከአምላክነቱ ያልተነጠለ ልጅነቱን መካድ፦ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰውነቱ የተናገረውንና የተነገረለትን ልክ ለመለኮቱ እንደ ተነገረ ተቈጥሮ ሲካድ እንመለከታለን። ለዚህም እንደ ዋቢ አድርገው የሚጠቅሱት፣ “የክርስቶስን ከዘላለም የእግዚአብሔር ልጅ አለመኾኑን” ኹለት ሃሳቦችን በአንድነት በመስፋት ነው። እንዲህ በማለት፦

Thursday, 25 June 2020

የእምነት እንቅስቃሴ አገልጋዮች፣ የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣን አይቀበሉም!


በቃለ አዋዲ የዘመኑ መልክ ላይ የእምነት እንቅስቃሴ አማኝና አገልጋዮች የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣን የማይቀበሉ መኾናቸውን እንዲህ አውግተን ነበር! ተከታተሉት!

Wednesday, 24 June 2020

ድንገት እንዳይደፋን!

Please read in PDF

ትንሺቱ አዚም እጀ ሰብዕ ጥንቆላ
እንዴት ቀዬአችንን፤ እርሻችንን ትብላ?

Saturday, 20 June 2020

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፰ - የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF
8.   ምስክርነት፦ በሐዋርያት ሥራ ውስጥ ምስክርነት ከድፍረት ጋር በቀጥታ ተጠቅሶ እንመለከተዋለን፤ ሐዋርያት ሲጸልዩ እንዲህ ብለው ጸለዩ፣ “… ባሪያዎችህም ቃልህን በፍጹም ድፍረት መናገር እንዲችሉ አድርጋቸው” በማለት፣ “ከጸለዩም በኋላ የነበሩበት ስፍራ ተናወጠ፤ ሁሉም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ፤ የእግዚአብሔርንም ቃል በድፍረት ተናገሩ።” (ሐዋ. 4፥29፡ 31)፤ አስቀድሞም ወንጌልን ይመሰክሩ የነበሩት በድፍረት፤ ያለ አንዳች ፍርሃትና መሸማቀቅ ነበር፤ (2፥29፤ 4፥13)።

Wednesday, 17 June 2020

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፯)

Please read in PDF
  6.      እግዚአብሔርን መምሰል፦ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረን፣ የእነርሱ መልክ ከበግ ጋር የተቀራረበ የተኩላ መልክ ነው፤ በበጎች መካከል ኾነው ይጸልያሉ፤ ይማራሉ፤ ያስተምራሉ፤ የበግ ጠባይ የያዙ መስለው ይመላለሳሉ። ዓላማቸው በጉን ለራሳቸው መንጠቅና በእረኛው እንዳያርፍ ማባዘንና ማቅበዝበዝ ነው።

Saturday, 13 June 2020

ባላንጣዎቹ ደቀ መዛሙርት

Please read in PDF

ጌታ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን የጠራቸው እጅግ ከተለያየ ቦታና ከተለያየ የሥራ ገበታቸው ነው። የአንዳንዶቹ ተግባራት ፈጽሞ የሚያቀራርባቸው ብቻ ያይደለ ደም የሚያቃባቸውም ጭምር እንደ ነበር ታሪካዊ ዳራዎችን ስናጠና ማስተዋል እንችላለን። ለዚህም በምሳሌነት ከአሥራ ኹለቱ መካከል ኹለቱን ደቀ መዛሙርት በማንሳት እንችላለን።

ከኢየሱስ ጥሪ በፊት

  ቅዱስ ማቴዎስና ቀናተኛው ስምኦን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከጠራቸው ቅዱሳን ደቀ መዛሙርት መካከል ናቸው፤ ማቴዎስ የተጠራው ከቀራጭነት ቦታ ሲኾን (ማቴ. 9፥9)፣ ቀናተኛው ስምዖን ደግሞ በቅጽል ስሙ እንደ ተጠራው ቀናተኞች ከኾኑት አይሁድ መካከል ነው። ማቴዎስ አይሁዳዊ ቢኾንም ለሮማውያን ተቀጣሪ በመኾኑና ግብርን ከአይሁድ ተቀብሎ ለሮማውያም በመሰብሰቡ በአይሁድ ዘንድ ፈጽሞ የተጠላ ነው። የትኞቹም አይሁድ ለሮማውያን የሚሠሩ አይሁድን የሚመለከቱት እንደ ከዳተኛና ከአሕዛብ ጋር እንደሚተባበሩ ነው።

Friday, 12 June 2020

የሐሰት መምህራን የማይነኳቸው ርእሶች (ክፍል ፮)

Please read in PDf

5.      ስቀሉን፦ ኀጢአተኛና የወደውን ዓለም ባለመናቅ፣ ኀጢአትን ፍጹም በመጥላትና በመጠየፍ፣ እግዚአብሔር ዓለምን ለማዳን አንድያ ልጁን በመስቀል አሳልፎ ሰጠ። በአዲስ ኪዳን ምንባባት ውስጥ ከሦስት መቶ በላይ የመስቀልን ትርጉሞችን ያስቀምጥልናል፤ በሌላ ንግግር የኀጢአት መገኘት፣ ፍርድና የኀጢአት ኃይል በተጠቀሰበት የአዲስ ኪዳናት ምንባባት ውስጥ ኹሉ፣ ነገረ መስቀሉ በአብዛኛው ተያይዞ እንደ ተጠቀሰ እናስተውላለን።

Sunday, 7 June 2020

ጰራቅሊጦስ

Please read in PDF
በምድር ዳርቻ ፍጹም ምድረ በዳ
ደግሞ በእልፍኜ በውስጤ ውስጥ ጓዲያ
በመከራ ሰዓት በመከሩ ደስታ

Friday, 5 June 2020

ድኃ አገልጋዮችና “ሃብታም” አገልጋዮች


  ልከኛ አገልጋይ፣ በሰማይና በምድር ሥልጣን የተሰጠው የጌታ ኢየሱስ ኹነኛ መልእክተኛ ነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ደቀ መዛሙርቱን የላከው የሰማይ አምባሳደር አድርጎ በመሾም ነው፤ (2ቆሮ. 5፥20)። ሰፊው መከር፣ ወንጌል በመስማት የሚድኑ አማንያን እንደ ኾኑ እንዲኹ፣ መከሩን ለማገልገል የሚያስፈልገው በረከትና አቅም ደግሞ እዚያው በረከት ውስጥ ያለ መኾኑን እናስተውላለን። ጌታ ኢየሱስ፦ “መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዲህ የመከሩን ጌታ ወደ መከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት” በማለት ደቀ መዛሙርቱን አዘዛቸው፤ (ማቴ. 9፥፥38)።

Wednesday, 3 June 2020

ሰዶማዊነት በኢትዮጵያ፣ ከኮሮና በፊት አልነበረምን?

Please read in PDF
    የትኛውንም የሕፃናት ሰቆቃ መስማት ያማል፤ ያስደንግጣል፤ ልብ ይሰብራል። በተለይም የቀኖቹ ክፋትና ዓመጽ፣ የምድሪቱን እርጅናና መወየብ አጉልቶ ከማሳየቱ ባሻገር፣ ሰዎች በሰዎች ላይ የሚያደርሱት ጭካኔና መራርነት እጅጉን አስፈሪ ኾኖአል። ግን እንዴት ችለን ይኾን የወለድናቸውን ሕፃናት፣ ቅርጥፍ አድርገን ስንበላ የጣፈጠን? እንዴት ቻለ አንጀታችን? የሰቈቃውን ስቃይ እየሰማን እንዴት አስቻለን? አውሬʼኮ የገዛ አውሬውን ስቃይ ይሰማል፤ ይራራልም፤ እንዴት እንዲህ ደበስን?!

Friday, 29 May 2020

ለኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን “መከፋፈል” ጊዜው ነውን?

Please read in PDF

  ከወደ ጐጃም የተሰማው ዜና መልካም አይመስልም፤ ቅብዐቶች ከኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አንድነት በመለየት የራሳቸውን አገረ ስብከት በመመስረት፣ ጳጳሳት መሾማቸው እየተሰማ ነው። ነገር ግን ይህ ምሳሌነቱ መልካም አይመስልም። በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ፕሮቴስታትንት ወይም ሐድሶአውያን ተብለው የማይወገዙ፣ ቢያንስ አራት ትምህርቶች አሉ፤ ቅብዐት፣ ጸጋ፣ ዘጠኝ መለኮትና ካራ፤ እኒህ ኹለቱ የትምህርት ይትበሃሎች ለዘመናት በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ [ከተወሰኑ ግጭቶች በቀር] በአብሮነት አሉ።

Wednesday, 27 May 2020

ዕርገቱ - የቤዝወታችን ፍጻሜና ተስፋችን!

Please read in PDF
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ማረጉ ባለፈው ሳምንት በምዕራባውያን አብያተ ክርስቲያናት፤ በዚህ ሳምንት ደግሞ በምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ዛሬ ይታሰባል፤ ዕርገቱን አንዱ ወንጌላዊ፣ በመንፈስ ቅዱስ መነዳት ኹለት ጊዜ ዘግቦልናል፤ ሉቃስ ወንጌላዊው፤ (ሉቃ. 2450-52 ሐዋ. 16: 11) ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱም ስለ ዕርገቱ አስቀድሞ ተናግሮአል፤ (ዮሐ. 142: 13 2017) ነቢያትም ትንቢት ተናግረውለታል፤ (ዳን. 79-13)

Sunday, 24 May 2020

“እመቤቴ ቤዛ ብትኾን ምንድር ነው?” (የማያልቀው የዶ/ር ዘበነ ለማ ተረት)

Please read in PDF

   ዶ/ር ዘበነ ለማ፣ በአገረ አሜሪካ የሬዲዮ ፕሮግራም አለው፤ ከጠያቂዎች ለሚመጣለት ጥያቄ ኹሉ መልስ የሚመልስበት። ትኩረቴን ከሳበውና ለዛሬ እንዳካፍላችሁ የፈለግኹት፣ በአንዲት እህት አማካይነት፣ በቤዛነት ዙሪያ የተጠየቀውንና የመለሰውን መልስ በማንሣት ይኾናል፤ የተዘጋጀው “የመናፍቃን ምላሽና የዶ/ር ቀሲስ መምህር ዘበነ ለማ መልስ ክፍል 6” በሚል ርእስ ነው። ለቀረበለት ጥያቄ ዘበነ የመለሰው፣ ጭምቀ ዐሳብ በአጭሩ እንዲህ የሚል ነው፦



Friday, 22 May 2020

ከ"ምኞት" ወይም ከ"ጉምዠታ" ወንጌል ተጠንቀቁ!


የብልጽግና ወንጌል መምህራን ብዙዎችን ካታለሉበት መንገድ አንዱ፣ ሥጋዊ አምሮትንና መሻትን ባልሞተው አዳም ውስጥ በማስገባት እና በመቀርቀር ነው። ይህ መንገድ ደግሞ ከዚህ ቀደም ሰይጣን ራሱ ያደረገውና ብክለትን ወደ ሰው ያስገባበት ጥበቡ ነው። በኢየሱስ ላይ ዓይኖቹ ትክ ያላሉ ኹሉ፣ በዚህ ጥበብ መታለሉ አይቀርም።