Monday, 23 March 2020

ስለ ተላላፊ በሽታ መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

Please read in PDF
መግቢያ
   ጌታችን ኢየሱስ መድኀኒት አስፈላጊነቱ ለበሽተኞች መኾኑን ተናገረ (ማቴ. 9፥12)፤ ስለዚህም ሰዎች ከበሽታ ለመዳን መድኀኒትን መጠቀማቸውን እናስተውላለን፤ “በጥንት ዘመን ሰዎች በመድኃኒት ሲያምኑ በነፍስ ሊበረቱ ይችላሉ። ጥቅሙ ከእምነት እንጂ ከመድኃኒት አልነበረም። ዛሬ ግን ብዙ ጊዜ በመድኃኒት ቢያምኑም ባያምኑም መድኃኒቱ ፍቱን ነውና ይሠራል”። ከፊት ዘመን ይልቅ በዛሬ ዘመን ሰዎች በመድኃኒት አብዝተው የሚታመኑ ይመስላል፤ ለዚህም ይመስላል በምድራችን ላይ እጅግ ዝቅተኛ ከሚባሉት እስከ ቅንጡ መታከሚያ ቤቶች የተበራከቱት። ነገር ግን ይህ ኹሌ ስሙርና የመጨረሻ መፍትሔ ኾኖ አይታይም።

Saturday, 21 March 2020

ደብረ ዘይት - ይመጣል ኢየሱስ

Please read in PDF

ርኩሰት እንዳየለ ሞት እንደ በረታ
ዓመጽ ገደብ አልፎ ኹሉን እንደ ረታ
የደዌ ነጋሪት የሕመም ጉሰማ

Wednesday, 18 March 2020

ተጽናኑ፤ አጽናኑም!

Please read in PDF

   አዲስ ኪዳን በአጭር ቃል፣ ከሥጋ ሕመምና ሞት፤ ከበሽታም ይልቅ ከእግዚአብሔር አባትነት መለየትና መነጠልን የዘላለም ሞትና ፍርድ እንደሚያስከትል ያስተምራል። የሥጋ ሕመምና ሞት በአዲስ ኪዳን ትምህርት፣ ጊዜያዊና ሰው የመኾናችን ውጤት መኾኑን ብቻ የሚያመለክትም ነው። ከዚህ ባሻገር ሰዎች ባለመታዘዝ በጸኑ ልክ፣ ለኀጢአት፣ ለዓመጻና ለማይረባ አእምሮ ተላልፈው ሊሰጡ ይችላሉ።


Sunday, 15 March 2020

ልበ መጻጉዕ!

Please read in PDF

   የዓቢይ ጾም አራተኛው ሳምንት ስያሜው መጻጉዕ ነው፤ ትርጉሙ በ ቁሙ ጐባጣ ማለት ነው። የስያሜው ታሪክ በቀጥታ የተያያዘው በዮሐንስ ወንጌል ምዕ. 5 ላይ ያለውን ታማሚ ሰውን ማዕከል ያደረገ ነው። ታማሚው ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ያህል ሕመምተኛ የነበረ ሰው ነው። ሕመሙ ምን እንደ ኾነ አልተጠቀሰም፤ ነገር ግን ጽኑ ሕመም መኾኑ አይካድም። በኢየሩሳሌም፣ በበጐች በር አጠገብ፣ አምስት ባለ መጠለያ መመላለሻዎች የነበሯት፣ በአራማይክ ቋንቋ ቤተ ሳይዳ ወይም ቤተዛታ ተብላ በምትጠራው የመጠመቂያ ስፍራ፣ ይህ መጻጉዕ ሰው ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ያህል ፈውስን ሲጠብቅ ኖሮአል።


Thursday, 12 March 2020

Monday, 9 March 2020

ምኩራብ - ሦስተኛው ቤተ መቅደስ

Please read in PDF

  ያለንበት የዓቢይ ጾም ሳምንት በማኅሌታይ ያሬድ ስያሜ፣ “ምኩራብ” ተብሎአል፤ ምኩራብ አይሁድ በምርኮ ወደ ባቢሎን በተወሰዱ ወራት፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን ለማንበብና የሕጉን ቃሎች ለማሰብ፣ በየጥቂት አባወራ በመሰባሰብ የጀመሩት ነው። ወደ አገራቸው ሲመለሱም ይኸንኑ በመቀጠል፣ ከዋናውና መሥዋዕት ከሚቀርብበት መቅደስ ባሻገር፣ በየመንደራቸው አቅራቢያ ምኩራብ በመሥራት፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማጥናትና ማንበብን በዚያ ጀመሩ። እንግዲህ ማኅሌታይ ያሬድ፣ ምኩራብን ለዓቢይ ጾም ሦስተኛው ሳምንት ሲሰይም፣ በሳምንቱ ውስጥ ከሚነበቡት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ደግሞ፣ ዮሐ. 2፥12-22ን በመመደብ ነው። ክፍሉም በቀጥታ በኢየሩሳሌም ከነበረው ቤተ መቅደስ ጋር በማያያዝ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረው ስለ መኾኑ የታመነ ነው።

Sunday, 8 March 2020

በእኔ የተናገርክ … ተባረክ!

Please read in PDF

አገልግሎትን በክብር መጨረስ መታደል ነው። ያለ መንፈስ ቅዱስ ዕርዳታም፣ ማንም አገልግሎቱን በክብር መጨረስ አይቻለውም። ሩጫውን ስለ ጨረሱ ቅዱሳን ስናስብ፣ ልባችን ታላቅ ሐሴት ያደርጋል፤ በመደነቅም ይሞላል፤ ኹላችን እንዲህ ብንኾን፣ በሕይወት ዘመናችን እንደ እነርሱ ባለ ትጋት ጸንተን፣ እርግጠኞች ኾነን፣ “መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤” ማለት ብንችል እንዴት በታደልን?! … አዎን! ለዚህ ተጠርተናል!!!

Wednesday, 4 March 2020

በማንቂያ ደወል አንቅተንስ … ?!

Please read in PDF

  ባለንበት ወር “የማንቂያ ደወል” የሚሉ ጉባኤያት፣ በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን በተደጋጋሚ ከአድባራት እስከ ደብራት ሲደረጉ እያየን ነው። ከተለያዩ ጉባኤያት “መምህራን” አንደበት እንደ ሰማነው፣ የጉባኤያቱ መነሻ ዐሳብ፣ ሕዝቡን ስለ ሃይማኖቱ ማንቃት፣ በተለይ አኹን እየደረሰ ካለው ውጫዊና ውስጣዊ ተጽዕኖ በመከላከል፣ ሃይማኖቱን እንዲጠብቅና ከፍ ሲልም “ሰማዕት” እንዲኾን ማድረግ የሚሉና ሌሎችም ጽኑ አቋሞች አሉት። ነገር ግን ለጉባኤያቱ መደረግ እንደ ሥረ ምክንያት የተነሡትና እንደ ጭብጥ የተያዙት ዐሳቦች፣ ከክርስትና አስተምህሮ እጅግ የራቁና መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ ያላቸው አይመስሉም

Monday, 2 March 2020

ቅድስት - ኢየሱስ ከሰንበት ይበልጣል!

Please read in PDF

  “ሰንበት” የሚለው ቃል፣ በዕብራይስጥ ትርጉሙ ማቆም ወይም መተው ማለት ነው።[1] “ሰንበት … የዕለት ስም ሰባት፣ ሰባተኛ ቀን፤ ሰባተኛ ዓመት ማረፊያ ዕረፍት…”[2] ማለት ነው። በቀደመው ኪዳን ትእዛዝ መሠረት፣ “ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፤ አንተ፥ ወንድ ልጅህም፥ ሴት ልጅህም፥ ሎሌህም፥ ገረድህም፥ ከብትህም፥ በደጆችህም ውስጥ ያለ እንግዳ በእርሱ ምንም ሥራ አትሥሩ፤ …” (ዘጸ. 20፥10) እንዲል፣ ማናቸውም የኪዳኑ አማኝ፣ የዘወትር ሥራውን ትቶ ወይም በማረፍ በኹለንተናዊ መልኩ እግዚአብሔር አምላኩን በአምልኮ ለማክበር የሚጠቀምበት ቀን ነው፤ የሰንበት ቀን ለዕረፍትነት ወይም ለአምልኮ መሰጠቱ ከሕጉ በፊት መኾኑን አለመዘንጋት፣ ለኹሉ የሰው ዘር መሰጠቱን እንድናስተውል ያደርገናል

Wednesday, 26 February 2020

ቤተ ክርስቲያንንም ለ“መደመር”?፤ ተዉ!

Please read in PDF

   በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ነገሥታት “በዶግማና በቀኖና” አንድ ያልነበሩትን “አብያተ ክርስቲያናት”፣ አንድ ለማድረግ እጅግ መጣራቸውን እናስተውላለን።


   “ከኬልቄዶን ጉባኤ በኋላ ለሚቀጥሉት ፩፻፶ ዓመታትያህል የነገሡ የቊስጥንጥንያ ነገሥታት ቤተ ክርስቲያንን ለማዋሐድ ብዙ ጥረት አድርገዋል። ለምሳሌ ከ፬፻፸፬-፬፻፺፩ ዓ/ም የነገሠው ዘይኑን(ዚኖን)፣ ከ፬፻፺፩-፭፻፲፰ዓ/ም የነገሠው እናስታሲዮስ በተዋሕዶ አንድ ባሕርይ የሚለውን የተዋሕዶ እምነት ተቀብለው ቤተ ክርስቲያን በሰላም የምትመራበትን መንገድ ለመፈለግ ተነሳሰተው ነበር። ለዚህም በጎ ፈቃድ መሰናክሉ የኬልቄዶን ጉባኤ ውሳኔና የልዮን ጦማር መኾኑን በመገንዘብ የቊስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳስ አባ አጋግዮስ(አካኪዮስ) እና ንጉሡ ዘይኑን ተስማምተው ይህን ለመሰረዝና ቤተ ክርስቲያንንም ወደ ጥንታዊ የተዋሕዶ እምነቷ ለመመለስ ከአንጾኪያና ከእስክንድርያው ፓትርያርኮች ጋር ውይይት ጀመሩ።”[1]

Thursday, 13 February 2020

በነነዌ ማግስት!

Please read in PDF

በነነዌ ምድር …
ኀጢአት ተከተተ፣ ነውር ተከደነ
ዓመጻ ታለለ፣ ምሕረት ገነነ

Thursday, 6 February 2020

ንቀት (ክፍል ፲ እና የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF
እንኪያስ፦
1.      ትናናቁ፦በማንኛውም የኑሮ ዘይቤ የሚኖሩ ሰዎችን ስታከብሩ፣ ሠሪያቸውን ወይም የፈጠራቸውን ያህዌ ኤሎሂምን ነው የምታከብሩት። እግዚአብሔር ሰውን ወደዚህ ምድር ሲያመጣው በትልቅ ዓላማና ለክብሩ መገለጫ ይኾን ዘንድ ነው። እኛ እንደ ሳይንቲስቶች ወይም እንደዚህ ምድር ጠቢባን በፈጠረው ዓለምና ሰው እጅግ በመደነቅና በመመሰጥ የምንዋጥና በዚህ ብቻ የምንቀር አይደለንም፤ ይልቁንም እግዚአብሔር ዓለምንና ሰውን የፈጠረው ያህዌ ኤሎሂም ከሰው ጋር ግላዊና ኅብረታዊ ግንኙነትን ሊመሠርት እንዳለው እናምናለን።

Wednesday, 5 February 2020

ንቀት (ክፍል ፱)

Please read in PDF

ኢየሱስ ክርስቶስ ዋናው አብነታችን!
ጌታችን ኢየሱስ ፍጹም ተንቆአል!
በአንድ ወቅት በክርስቶስ ኢየሱስ ጉዳይ በአይሁድ ሸንጐና ሕዝብ ክርክር መደረጉን፤ በመካከላቸው መለያየት በተደጋጋሚ መከሰቱንም የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል ይነግረናል፤ (7፥43፤ 9፥16፤ 10፥19)።ለዚህ ምላሽ እንዲኾንም የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ለማስያዝ ያደረጓቸው ተግባራት ለኢየሱስ የነበራቸውን ንቀት ፍንትው አድርጐ ያሳያል። ዮሐንስ ይህን በሚገባ ይገልጠዋል፤ አስቀድሞ እነርሱ ከሚያከብሩአቸው ሰዎች ታላላቅ ሰዎችን በመላክ ለኢየሱስ ያላቸውን አክብሮት ቢያሳዩም፣ በኋላ ላይ ግልጹ ዐሳባቸው ታውቆአል፤ ይኸውም ለኢየሱስ ያላቸውን ንቀት ለማሳየት ጠባቂዎችንና ዝቅተኛ ሥልጣን ያላቸውን ሰዎች ልከዋል፤ ነገር ግን ከፊተኞቹ የኒቆዲሞስ ማመን ከኋለኞቹም ጠባቂዎች “እንደዚህ ሰው ማንም እንዲሁ ከቶ አልተናገረም” የሚል ምስክርነት መገኘቱ እጅግ የሚደንቅ ነው፤ (ዮሐ. 7፥45-52)።

Sunday, 2 February 2020

ንቀት (ክፍል ፰)

Please read in PDF
1.    በአገራችን አስተዳደጋችን ምንታዌነት አለው
   በመጀመሪያቱ ቤተ ክርስቲያን ቤተሰቦች ውስጥ የነበሩት ባሪያዎች፣ አንዳንዶቹ በጌታ ኢየሱስ ያመኑ ነበሩ፤  ስለዚህም እኒህን ባሪያዎች እንደ ወንድሞቻቸው እንጂ እንደ ቤት አገልጋዮቻቸው እንኳ አይመለከቱአቸውም ነበር፤ ነገር ግን እኒህ ባሪያዎች በተቃራኒው ጌቶቻቸውን መናቅ ጀመሩ፤ የክርስትናው ነጻነት ይበልጥ ሊያከብሩአቸውና ሊሠሩላቸው እንዲገባ ማዘዙን ዘነጉት፣ እነርሱ ግን በተቃራኒው አደረጉ። አንድ አገልጋይ በግዴታ ያገለግል በነበረበት ወራት ይሠራ የነበረውን ሥራ ኹሉ፣ አኹን ግን በፍቅር መሥራት ተሳነው። ለዚህ ነው ቅዱስ ጳውሎስ፦
የሚያምኑም ጌቶች ያሉአቸው፥ ወንድሞች ስለሆኑ አይናቁአቸው፥ ነገር ግን በመልካም ሥራቸው የሚጠቅሙ የሚያምኑና የተወደዱ ስለሆኑ፥ ከፊት ይልቅ ያገልግሉ።” (1ጢሞ. 6፥2)