Wednesday, 5 February 2020

ንቀት (ክፍል ፱)

Please read in PDF

ኢየሱስ ክርስቶስ ዋናው አብነታችን!
ጌታችን ኢየሱስ ፍጹም ተንቆአል!
በአንድ ወቅት በክርስቶስ ኢየሱስ ጉዳይ በአይሁድ ሸንጐና ሕዝብ ክርክር መደረጉን፤ በመካከላቸው መለያየት በተደጋጋሚ መከሰቱንም የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል ይነግረናል፤ (7፥43፤ 9፥16፤ 10፥19)።ለዚህ ምላሽ እንዲኾንም የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ለማስያዝ ያደረጓቸው ተግባራት ለኢየሱስ የነበራቸውን ንቀት ፍንትው አድርጐ ያሳያል። ዮሐንስ ይህን በሚገባ ይገልጠዋል፤ አስቀድሞ እነርሱ ከሚያከብሩአቸው ሰዎች ታላላቅ ሰዎችን በመላክ ለኢየሱስ ያላቸውን አክብሮት ቢያሳዩም፣ በኋላ ላይ ግልጹ ዐሳባቸው ታውቆአል፤ ይኸውም ለኢየሱስ ያላቸውን ንቀት ለማሳየት ጠባቂዎችንና ዝቅተኛ ሥልጣን ያላቸውን ሰዎች ልከዋል፤ ነገር ግን ከፊተኞቹ የኒቆዲሞስ ማመን ከኋለኞቹም ጠባቂዎች “እንደዚህ ሰው ማንም እንዲሁ ከቶ አልተናገረም” የሚል ምስክርነት መገኘቱ እጅግ የሚደንቅ ነው፤ (ዮሐ. 7፥45-52)።

Sunday, 2 February 2020

ንቀት (ክፍል ፰)

Please read in PDF
1.    በአገራችን አስተዳደጋችን ምንታዌነት አለው
   በመጀመሪያቱ ቤተ ክርስቲያን ቤተሰቦች ውስጥ የነበሩት ባሪያዎች፣ አንዳንዶቹ በጌታ ኢየሱስ ያመኑ ነበሩ፤  ስለዚህም እኒህን ባሪያዎች እንደ ወንድሞቻቸው እንጂ እንደ ቤት አገልጋዮቻቸው እንኳ አይመለከቱአቸውም ነበር፤ ነገር ግን እኒህ ባሪያዎች በተቃራኒው ጌቶቻቸውን መናቅ ጀመሩ፤ የክርስትናው ነጻነት ይበልጥ ሊያከብሩአቸውና ሊሠሩላቸው እንዲገባ ማዘዙን ዘነጉት፣ እነርሱ ግን በተቃራኒው አደረጉ። አንድ አገልጋይ በግዴታ ያገለግል በነበረበት ወራት ይሠራ የነበረውን ሥራ ኹሉ፣ አኹን ግን በፍቅር መሥራት ተሳነው። ለዚህ ነው ቅዱስ ጳውሎስ፦
የሚያምኑም ጌቶች ያሉአቸው፥ ወንድሞች ስለሆኑ አይናቁአቸው፥ ነገር ግን በመልካም ሥራቸው የሚጠቅሙ የሚያምኑና የተወደዱ ስለሆኑ፥ ከፊት ይልቅ ያገልግሉ።” (1ጢሞ. 6፥2)

Saturday, 25 January 2020

“እኔነቴ”ን ልውደድ!

Please read in PDF

ራሴን አልወድም
አንተ ባየኸኝ ልክ “እኔ እኔን” አላይም
እናማ ጌታዬ!

Wednesday, 22 January 2020

ንቀት (ክፍል ፯)

ለምን ግን እንናናቃለን?
   አንዳንዶች በመልካቸው ብቻ ይናቃሉ፤ ለምሳሌ፦ በዓረብ ማኅበረ ሰብ ውስጥ ያሉ ጥቁር ዓረቦች፣ ጥቁር ስለኾኑ ብቻ የተናቁ እንደ ኾኑ ይናገራሉ፤[1] አንዳንድ “ቤተ እምነቶች” ንቀትን የማበረታታት ትምህርቶች አላቸው፤ ለምሳሌ፦ ከእነርሱ ቤተ እምነት ውጪ ያሉትን ወይም የቤተ እምነታቸውን ቀኖናና ዶግማ የማይቀበሉትን ማናቸውንም ቤተ እምነቶች መናቅ እንደሚገባቸው ያምናሉ፤ ልክ አብዛኛዎቹ የፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናት ወይም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አንዳቸው ሌላውን እንደሚንቁ። እንዲያውም እንደ እስልምና[2]፣ ጅሖቫ፣ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት፣ የእምነት ቃል አገልግሎት፣ ሞርሞንና ተመሳሳይ “ቤተ እምነቶች”፣ ማንኛውም ሰው የእነርሱን ቤተ እምነት ቀኖናና ዶግማ ካልተቀበለና ከእነርሱ ውጭ ካለው ማናቸውም ኅብረት ጋር፣ ኅብረት ቢያደርግ “ከርኩሱ ዓለም ጋር ግንኙነት እንዳደረገ ወይም እንደ ተካፈለ” አጥብቀው ያስተምራሉ።

Sunday, 19 January 2020

በጥምቀቱ ከኀጢአተኞች ጋር ተቈጠረ!

Please read in PDF
 
   ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጠመቁን ነገር በየዓመቱ በኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት “ታስቦ” ይውላል፤ መታሰቡ “መልካም” ቢኾንም፣ የሚታሰብበት መንገድ ግን ፈጽሞ ከመጽሐፍ ቅዱስ መራቁ፣ እጅግ የሚደንቅ የሚያሳዝንም ነው። በአገራችን “በዓለ” ጥምቀት አብዛኛውን ጊዜ ከመንፈሳዊ ነጸብራቅነቱ ይልቅ፣ ባሕላዊና ʻሃይማኖታዊ ሥርዓት መከናወኛ ብቻ ኾኖ ሲከበርʼ እናስተውላለን። ጭፈራ፣ ሽለላ፣ ʻታቦትʼ እጀባ፣ ሎሚ ውርወራ፣ የአዳዲስ ልብስ ማሳያና … ሌሎችም ተግባራት፣ ልኩንና ገደቡን በጣሰ መልኩ የሚቀርቡት በዚሁ በጥምቀት “በዓል” ቀን ነው። ቤተ ክርስቲያን ወደ ኢየሱሳዊ መንፈሳዊነት ፍጹም አለማዘንበልዋ እንዲህ ላለ ሰፊ ተላላነት ተላልፋ መሰጧን ማስተዋል አያዳግትም።

Thursday, 9 January 2020

ጠላቱን ወዳዱ!

Please read in PDF
አዳም!
የሞተው በኀጢአት የተንኮታኮተው፣
ከሰውነት ማማ አዘቅት የወረደው

Monday, 6 January 2020

የእግዚአብሔር ቅንአት!

Please read in PDF
የእግዚአብሔር ቅንዓት ይህን ያደርጋል።”
   ነቢየ ልዑል ኢሳይያስ፣ ሕጻኑ ወንድ ልጅ ጌታ ኢየሱስ ከርስቶስ ለእኛ በውድ ስጦታነት እንደ ተሰጠ ይነግረናል። “ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤” በማለት አብ ብዙ ስጦታዎችን ለእኛ ሰጥቶናል፤ ኢየሱስን የሚያህል ስጦታ ግን አልሰጠንም፤ ወደ ፊትም አይሰጠንም፤ የተሰጠን የትኛውም ስጦታ ከኢየሱስ አይበልጥምና። አስቀድሞ በራሱ መልክና ምሳሌ ፈጥሮን፣ የራሱን መልክና አምሳል በእኛ በማኖር ክብሩንና ጽድቁን፣ ዕውቀቱንና አለመሞትን ለኹላችን አድሎናል። እግዚአብሔር ሰውን ቅዱስ አድርጎ በመፍጠሩም፣ ከሌሎች ፍጡራን በተለየ መልኩ፣ ሰው የእግዚአብሔርን ቅድስና ተካፋይ ኾነ።


Tuesday, 31 December 2019

ንቀት (ክፍል ፮)

Please read in PDF

ሌሎችን በመናቃቸው ምክንያት የወደቁ ሰዎች

  መጽሐፍ ቅዱስ አያሌዎች ሌላውን በመናቃቸው ምክንያት መውደቃቸውንና መንኮታኮታቸውን በግልጥ ያስተምረናል፤ በዓለም ላይ ከተከናወኑ ጥቂት ያይደሉ ታሪኮች ውስጥ እንኳ፣ ገናና የተባሉትንና ያልተጠበቁትን ሲያዋርድ ተመልክተናል፤ አንብበናል። በተለይም “ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር” የተጻፈልን ሕያው የእግዚአብሔር እስትንፋስ የኾነው መጽሐፍ ቅዱስ፣ በንቀታቸው ምክንያት ስለወደቁት ሰዎች እንዲህ ያስተምረናል፦
1.    የጎልያድ ንቀት
  መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ጎልያድ የጦር ትጥቅ እንዲህ በማለት ይናገራል፤ “… የጌት ሰው ጎልያድ፥ ቁመቱም ስድስት ክንድ ከስንዝር የሆነ፥ ዋነኛ ጀግና መጣ። በራሱም የናስ ቍር ደፍቶ ነበር፥ ጥሩርም ለብሶ ነበር፤ የጥሩሩም ሚዛን አምስት ሺህ ሰቅል ናስ ነበረ። በእግሮቹም ላይ የናስ ገምባሌ ነበረ፥ የናስም ጭሬ በትከሻው ላይ ነበረ። የጦሩም የቦ እንደ ሸማኔ መጠቅልያ ነበረ፤ የጦሩም ሚዛን ስድስት መቶ ሰቅል ብረት ነበረ።” ጎልያድ እንዲህ ያለ አለባበስ በመልበሱና የውጊያ ትጥቅን በመታጠቁ፣ ከፍልስጥኤማውያን ኹሉ አንደኛ አድርጎታል፤ በዚህ ሳይበቃ እስራኤልንና ንጉሡ ሳኦልንም ጭምር በማንቀጥቀጡ የሚደርስበት ፈጽሞ አልተገኘም።


Wednesday, 18 December 2019

“በክርስቶስ” - የመከር ሰዓት የመዝሙር መንፈሳዊ መከር!

Please read in PDF
ንደርደር
   መዝሙር ከሰማየ ሰማያት ከመላእክት ዓለም ወደ እኛ ተንቆርቁሮ ፈስሶ፣ ያራሰን ሰማያዊ ጠልና የምንመገበው መና ነው፤ መላእክት የዘላለም ደስታቸው ትዳርና ምድራዊ ብእል አይደለም፤ “እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ” እንደ ተባለው እንዲሁ፣ እኛም በፍጻሜአችን መንፈሳዊ አካል ስንለብስ፣ መንፈሳዊ ቅኔና መዝሙር ተቀኚና ዘማሪ ነን፤ “እነሆ፥ የእግዚአብሔር ድንኳን በሰዎች መካከል ነው ከእነርሱም ጋር ያድራል፥ እነርሱም ሕዝቡ ይሆናሉ እግዚአብሔርም እርሱ ራሱ ከእነርሱ ጋር ሆኖ አምላካቸው ይሆናል፤” በተባለው በበጉ ሰማይ ላይ ፣ የማያቋርጥና የማያባራ አስደማሚና አስደናቂ ምስጋናና ዝማሬ አለ!!!

Monday, 16 December 2019

ጌታን አትስቀሉ!

Please read in PDF
ሞት ክፋት ጭንገፋ
ርስቱ እንዳይሰፋ
ኃጢአት እድፈት ርኩሰት
ነግሠው እንዳይገዟት

Thursday, 12 December 2019

ንቀት (ክፍል ፭)

Please read in PDF

እግዚአብሔርን የሚንቁ ይናቃሉ!

   እግዚአብሔር ኹሉን በሉዓላዊ ሥልጣኑ ተቈጣጣሪና ገዢ አምላክ ነው፤ ደግሞም ራሱን ዝቅ አድርጐ የሰውን ልጅ ውድቀቱን፤ ውርደቱን ሳይጸየፍና ሳይንቅ በፍቅሩ የቀረበ ገናና ተወዳጅ አምላክ ነው፤ አስቀድሞ እኛን ሲፈጥረንና ከወደቅንም በኋላ ወደ እኛ የቀረበበት፤ ወደ እርሱም እኛን የሳበበት ዋነኛ ምክንያቱ ክብሩን እንድንገልጥ ነው። ከዚህ በተቃራኒ ብንቆም ግን በግልጥ የተነገረ ቃል አለ፤ “ያከበሩኝን አከብራለሁና፥ የናቁኝም ይናቃሉና” (1ሳሙ. 2፥30)።




Tuesday, 3 December 2019

ንቀት (ክፍል ፬)

Please read in PDF
የአይሁድና የሳምራውያን መናናቅ
    ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር በመጣበት ጊዜ የአይሁድና የሳምራውያንን ኹኔታ ወንጌላዊው ዮሐንስ እንዲህ በማለት ይገልጠዋል፤ “አይሁድ ከሳምራውያን ጋር አይተባበሩም ነበርና።” (ዮሐ. 4፥9)። በጥንት ታሪክ ሳምራውያን ከአይሁድ ጋር አንድ ነበሩ፤ ነገር ግን ከአሦር ምርኮ በኋላ፣
   “የአሦርም ንጉሥ ከባቢሎንና ከኩታ ከአዋና ከሐማት ከሴፈርዋይም ሰዎችን አመጣ፥ በእስራኤልም ልጆች ፋንታ በሰማርያ ከተሞች አኖራቸው፤ ሰማርያንም ወረሱአት፤ በከተሞችዋም ተቀመጡ። በዚያም መቀመጥ በጀመሩ ጊዜ እግዚአብሔርን አይፈሩትም ነበር፤ እግዚአብሔርም አንበሶች ሰደደባቸው፥ ይገድሉአቸውም ነበር። ስለዚህም ለአሦር ንጉሥ። ያፈለስኻቸው፥ በሰማርያም ከተሞች ያኖርኻቸው የአገሩን አምላክ ወግ አላወቁም፤ የአገሩን አምላክ ወግ አላወቁምና አንበሶችን ሰድዶባቸዋል፥ እነሆም፥ ገደሉአቸው ብለው ተናገሩት። የአሦርም ንጉሥ። ከዚያ ካመጣችኋቸው ካህናት አንዱን ውሰዱ፤ ሄዶም በዚያ ይቀመጥ፥ የአገሩንም አምላክ ወግ ያስተምራቸው ብሎ አዘዘ። ከሰማርያም ካፈለሱአቸው ካህናት አንዱ መጥቶ በቤቴል ተቀመጠ፥ እግዚአብሔርንም እንዴት እንዲፈሩት ያስተምራቸው ነበር። በየሕዝባቸውም አምላካቸውን አደረጉ፥ ሰምራውያንም በሠሩት በኮረብታው መስገጃዎች ሕዝቡ ሁሉ በሚኖሩበት ከተሞቻቸው አኖሩአቸው። … ከመካከላቸውም ለኮረብታው መስገጃዎች ካህናት አደረጉ፥ በኮረብታውም መስገጃዎች ይሠዉ ነበር።  እግዚአብሔርንም ሲፈሩ ከመካከላቸው እንደ ፈለሱት እንደ አሕዛብ ልማድ አምላካቸውን ያመልኩ ነበር። እስከ ዛሬ ድረስ እንደ ቀደመው ልማድ ያደርጋሉ፤ እግዚአብሔርንም አይፈሩም፥ እግዚአብሔርም እስራኤል ብሎ የጠራውን የያዕቆብን ልጆች እንዳዘዛቸው ሥርዓትና ፍርድ ሕግና ትእዛዝም አያደርጉም።  ” (2ነገ. 17፥22-29፤ 33-34)

Wednesday, 20 November 2019

ንቀት (ክፍል ፫)

Please read in PDF
ጌታ ኢየሱስ ማንንም አልናቀም!
  “… በተስፋ የተጠበቀው መሲሕ ሌላ ዐይነት ክብር፣ ማለትም የትሕትናን ክብር ለብሶ ነበር በመካከላቸው የተገኘው። አባ ኔቪል ፈጊስ የተባሉ ካህን እንደ ተናገሩት፣ ‘እግዚአብሔር ታላቅ ነው የሚለው የሙስሊሞች እወጃ እውነትነቱ ጉልህ በመሆኑ ያለልዕለ ተፈጥሮአዊ ህልው እገዛ ሰው ሊረዳው ይችላል። እግዚአብሔር ትንሽ ነው የሚለውን ግን ኢየሱስ ለሰው ልጆች ያስተማራቸው እውነት ነው’ …”[1]
   ጌታ ኢየሱስ ወደ ምድር የመጣበት መንገድ እጅግ አስደናቂና ልብን በመደነቅ የሚመላ ነው። የመጣበት መንገዱና ዓላማው ለብዙዎች የሚጥምና የሚጣፍጥ አይደለም፤ በአዲስ ኪዳንም አገላለጥ ጠባብ መንገድ፣ የግመል መርፌ ቀዳዳ ታህል፣ እስከ መስቀል ሞት መታዘዝ፣ የራስ ክብርንና መብትን መተው፣ ባልንጀራን እንደ ራስ መውደድ … በሚል ውብ ሕይወትና ዝንባሌዎች የተመላ ነው።

Wednesday, 13 November 2019

ንቀት (ክፍል ፪)

Please read in PDF
እግዚአብሔር አይንቅም!
   እግዚአብሔር አምላክ በክብር የተከበበና በፍቅር የተትረፈረፈ አምላክ ነው፤ እግዚአብሔር ፍጥረትንም ሲፈጥረው በድንቅና በግሩም ክብር ነው፤ “ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ፤ ሥራህ ድንቅ ነው፥ ነፍሴም እጅግ ታውቀዋለች።” (መዝ. 139፥14) እንዲል፣ ሰው በግሩም፤ በድንቅ አድናቆት ተመልቶ የተፈጠረ ነው። መዝሙረኛው እንዲህ ሲል የፈጠርከውን ሰው የምታውቀው አንተ ነህ፤ እኔንም የፈጠርኸኝ አንተ ነህና በሚገባ ታውቀኛለህ፤ ምክንያቱም በእናቴ ማኅፀን ያበጃጀኸኝና በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ ንቁ ኾነህ የተንከባከብኸኝ አንተ ነህ እያለ ነው፣ ያህዌ ኤሎሂምን!