Please read in PDF
“ወንጌላውያን” ነቢያትና ቤተ
መንግሥታዊ ማስታወቂያነታቸው
“ወንጌላውያን” ነቢያትና ጥቂት የማይባሉ ኦርቶዶክሳውያን አገልጋዮችም
ጭምር ቤተ መንግሥቱ በሕዝብ ዘንድ ዕውቅና ያገኝ ዘንድ ተግተው “እያገለገሉ” ይመስላል፤ ለዚህም ለምሳሌ፦ ጠቅላይ ሚኒስቴሩ
መወቀስ አይገባቸውም እስከሚለው ጥግ የሄዱ አገልጋዮችን አይተናል፤ እንዲያውም ቤተ ክርስቲያን ከቤተ መንግሥት ባነሰ ማንነት
መኖሯን ራሳቸውን ጭምር በመስደብ ያቀረቡትን ሰምተናቸዋል። ለዚህም ለከት አልባ በኾነ መንገድ ግልጥ ፖለቲካዊ ቃላትን በመጠቀም
ሲወርዱ ተመልክተናቸዋል።
ለምሳሌ፦
- “አርበኝነት
በደሙ የተዋሐደው” ኢትዮጲያዊነት፣
- ሃያ
ሰባት ዓመታት መብታችን ተጥሶ … ፣
- የኢትዮጵያ
… የጠላቶቿ ድንጋይ አቀባዮች (የማርሲሉ ዮናታን አክሊሉ)፣
- ኢትዮጵያን
እግዚአብሔር በቃል ኪዳን ጠብቆአታል፣







