Tuesday, 1 August 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ አምስት)

Please read in PDf
የምንዋጋባቸው መሣርያዎቻችን
    መጽሐፍ ቅዱስ ከማን ጋር መዋጋት እንዳለብን አበክሮ የተናገረውን ያህል ከጠላታችን ጋር በመዋጋት በትክክል ስለምናሸንፍበት መሣርያም በግልጥ ይናገራል፡፡ ከዚህ በፊት እንዳየነው የምንዋጋው የእምነት ጦርነት ነው፡፡ የውጊያውም የጊዜ ቆይታ እስከክርስቶስ ዳግመኛ መምጣት ድረስ የሚቀጥል ነው፡፡ “በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታን ሆነን … የዲያብሎስን ሽንገላ መቃወም እንዲቻለን፣ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ መልበስ ያስፈልገናል”፡፡ ልብሱንና የጦር ዕቃውን መልበስና መለማመድ ግድ ነው፤ ያልተለማመድንበትና አብረን “ያልሰለጠንበት” ልብስ ለውጊያ ሊሆነን ፈጽሞ አይችልም፡፡
     የመሣርያው ዓይነት፣ የትጥቆቹ ይዘት በመከላከልና በማጥቃት ላይ የተመሰረቱ ናቸው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ሁለቱንም ሥራዎች[መከላከልና ማጥቃትን] ክርስቲያኖች መፈጸም እንዳለባቸው ያስተምራል፡፡ ለጌታ መታዘዝን በባርያ ማንነት ውስጥ ሆነን የምናሳየውን ትጋት ያህል፣ ለጠላትና ለሚያስጨንቀው ገዢ አለመታዘዛችንና ግልጥ ተቃውሞዓችንን የምናሳይበት መንፈሳዊ ጠባይ የጌታ መንፈሳዊ ወታደር በመሆን ነው፡፡

Tuesday, 18 July 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ አራት)

                                                                                   Please read in PDF
2. ዋጉ፦ በክርስቶስ ኢየሱስ ካመንንበት ቀን ጀምሮ ከክፋት ሁሉ አሠራርና ከዲያብሎስ ጋር ውጊያ ለመግጠም ፊት ለፊት ተፋጥጠናል፡፡ ደጋግመን እንዳነሣነው ውጊያችንም ከሥጋ ለባሽ ፍጡር ጋር ሳይሆን፣ ከጀርባው ለራሱ ክብርና አምልኮን ለመቀበል ከሚሠራው[ወንጌል የጨበጡ አገልጋዮችንም ጭምር በመጠቀም] ከክፉ መንፈሳውያን ሠራዊት አለቃ ከሆነው ከዲያብሎስ ጋር ነው፤ (ኤፌ.6፥12)፡፡ ውጊያውን በተመሳሳይ መንገድ በመቆም እንጂ በግል ማንነታችን ብቻ ማሸነፍ እንደማንችል መጽሐፍ ቅዱስ ደጋግሞ ነግሮናል፡፡
     “በሰው ልማድ ምንም እንኳ የምንመላለስ ብንሆን፥ እንደ ሰው ልማድ አንዋጋም፤ የጦር ዕቃችን ሥጋዊ አይደለምና፥ ምሽግን ለመስበር ግን በእግዚአብሔር ፊት ብርቱ ነው፤ የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን፤ ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን፤” (2ቆሮ.10፥3-5) እንዲል፣ ሰይጣን የሚሰወርበትንና የሚሰውርበትን የክፋትን ምሽግ፣ የስህተትን ትምህርት፣ ርኩሰትና ኃጢአትን ሁሉ ለማፍረስና ለመደምሰስ ፍጹም የሆነ ብቃት ያለውና ጠንካራው መሣርያ ከእግዚአብሔር የምናገኘው ጦር ዕቃ ብቻ ነው፡፡

Friday, 14 July 2017

ላ'ንተ ብቻ

የበገናው የመሰንቆው ኅብረ ዜማ
የዋሽንቱም የክራሩም የከበሮው ጥዑም ቃና
የግዕዛን ፉጨት የሕያዋን ቅኝት
የአምልኮ እልልታ የእንሰሳት የአራዊት
ላንተ ብቻ ይሁን ለክብር መንግሥትህ
ክብር ተጠቅልሎ አንተን ብቻ ያክብርህ!!!

Monday, 10 July 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ ሦስት)

Please read in PDf
3.    ይጣን፦ ብዙ ስሞች ያሉት ያሉት ሲሆን፣ ሰይጣን በዕብራይስጡ አሰናካይ፣ ስም አጥፊ፤ (ኢዮ.1፥6 ፤ ዘካ.3፥1 ፤ ማቴ.4፥10 ፤ ራእ.12፥9)፤ ዲያብሎስ ደግሞ ስም አጥፊ፣ ከሳሽ፤ ቤልሆር ማለት ደግሞ የማይረባ ከንቱ (2ቆሮ.6፥15)፤ አብዶንና አጶልዮንም አጥፊ (ራእ.9፥11) ተብሏል፤ በሌላ ሥፍራ ደግሞ የዚህ ዓለም ገዥ(ዮሐ.12፥311)፣ ወይም የዚህ ዓለም አምላክ (2ቆሮ.4፥11) ተብሎ ተጠርቷል፡፡ በተለይም ደግሞ ስለተንኮለኛነቱና አታላይነቱ የቀደመው እባብ ወይም ታላቁ ዘንዶ(ራእ.12፥9)፣ ዛቻ ወዳጅና የሚያስፈራራ ስለመሆኑ ደግሞ “የሚያገሳ አንበሳ” ተብሏል፤ (1ጴጥ.5፥8)፡፡
     ሰይጣን ዋና ዓላማው ሰዎች ለጌታችን ኢየሱስ ያላቸውን ትኩረት ማስነፈግ ነው፡፡ ትኩረታቸውንና ፊታቸውን ከኢየሱስ ዘወር ባደረጉ ጊዜ ለማን እንደሚያደሉና ወደማን እንደሚያቀኑ በትክክል ያውቀዋል፡፡ ይህንንም ለማድረግ ስውር መረቡን ይዘረጋል፡፡ የክፋት መረቡንም ለመዘርጋት የሚራዱ ብዙ ኃይላትና ሠራዊት፣ ተባባሪዎችም አሉት፤ (ኤፌ.6፥10)፡፡ ከዚህም ባሻገር ልናጣጥልና ልንንቀው የማንችለው የክፋት ጥበብንም የተመላ ነው፡፡

Friday, 7 July 2017

ዘፈን - የወደቀው መልአክ እንጉርጉሮ (የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF
እግዚአብሔር ዘፈንን አይባርክም!

    ከዘፋኞች በተደጋጋሚ የምናደምጠው፣ “እግዚአብሔር ዘፈናቸውን እንደሚባርክ፣ ለዘፈን የሚኾን ድምጽ እንደሰጣቸው፣ በመዝፈናቸው እግዚአብሔርም ጭምር ሊደሰት እንደሚችል፣ እንዲያውም ለመዝፈናቸውና ካሴት ለማሳተማቸው ጭምር እግዚአብሔር እንደረዳቸውና እንደባረከላቸው” ሳያፍሩ ሲናገሩ ይደመጣሉ፡፡ እኔን ብዙ ጊዜ እንደገባኝ ግን፣ “እግዚአብሔር” ሲሉ፣ ቅዱሱንና ለኃጢአት ልጁን አሳልፎ የሰጠውን እግዚአብሔርን፣ እግዚአብሔር ብለው እንደማይጠሩ በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ፡፡ ምክንያቱም በየትኛውም ዘመን ቅዱሱ እግዚአብሔር ከኃጢአት ጋር የተደራረደረበትና “ኃጢአትን የባረከበትን ሂደት” ሰምተንም፤ አይተንም አናውቅምና፤ ቅዱሳት መጻሕፍትም እንዲህ ያለውን ምስክርነት ፈጽመው አላስቀመጡልንም፡፡
     እግዚአብሔር ዘፈንን የሚባርክ ከሆነ፣ ከዘፈን ጋር የተጠቀሱትንም የሥጋ ፍሬዎች “ዝሙትን፥ ርኵሰትን፥ መዳራትን፥ ጣዖትን ማምለክን፥ ምዋርትን፥ ጥልን፥ ክርክርን፥ ቅንዓትን፥ ቁጣን፥ አድመኛነትን፥ መለያየትን፥ መናፍቅነትን፥ ምቀኝነትን፥ መግደልን፥ ስካርን፥ … ይህንም የሚመስለውን ሁሉ” መባረክ አለበት እያልን ነው፡፡ ሌላውን ሁሉ ጥሎ፣ ነጥሎ ዘፈንን ይባርካል ማለት፣ እግዚአብሔርን የስንፍና ሃሳባቸው ደጋፊ ለማድረግ ከማሰብ የመነጨ ተላላነት ነው፡፡ እንጂማ ዘፈን ከምንና ከማን ጋር እንደተጠቀሰ በትክክል ቢያነቡት፣ “እግዚአብሔር ዘፈንንም ይባርካል” በማለት እግዚአብሔር ላይ ለመሳለቅ ባልደፈሩ ነበር፡፡

Thursday, 29 June 2017

“እኔ” ሥልጣን ይጣ!

አርነት አታውጣኝ ለሥጋ ፈቃዴ፣
ነጻነት አትስጠኝ እንድሆን መደዴ፤
የቃልህን ብርሃን በዝቶልኝ ካየሁህ፣

Friday, 23 June 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ ሁለት)

Please read in PDF

2.    ኃጢአት፦ በዕብራይስጥ [ኀቻታ] በግሪክ ደግሞ [ሐማርቲያ] ተብሎ የተነገረ ቃል ሲሆን፣  በተካካይ የአማርኛ ትርጉሙ ደግሞ “ዒላማን መሳት” ተብሎ ተተርጉሟል፡፡ ይኸውም እግዚአብሔር እንድንደርስበት የሚፈልገው ዋና ዒላማና ግብ አለ፡፡ እዚያ እርሱ ካሰበበት መድረስ አለመቻል ዒላማን መሳትና ኃጢአት ነው፡፡
     የእግዚአብሔር ልጆች ዋና ዒላማችን እግዚአብሔር ራሱ ነው፤ ከእርሱ ፈቀቅ ማለት ቀስትን እንደሚስት ዒላማ ሳች (መሳ.20፥16)፣ እግሩን በማፍጠን ከእውነት መንገድ ይስታል፤ (ምሳ.19፥2)፡፡ በማንኛውም ሁኔታ ከእግዚአብሔር ያነሰ ዒላማ፣ ከእርሱ ያነሰ ግብም ሊኖረን አይገባም፡፡ ከእግዚአብሔር ያነሰ ዒላማ ካለን ግን፣ ያ የያዝነው ዒላማ መልካምም ቢሆን እንኳ ኃጢአት ነው፡፡

Sunday, 18 June 2017

ዘፈን - የወደቀው መልአክ እንጉርጉሮ (ክፍል 5)

Please read in PDF
በቋንቋው ተናጋሪ ሊቃውንት[1] ዘንድ ዘፈን ኃጢአት ነው!
      አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌም ሆነ ደስታ ተክለ ወልድም የዘፈንና የዘፋኝነትን ዓለማዊነት ወይም ኀጢአትነት በግልጥ አስቀምጠዋል፡፡ በመጽሐፎቻቸውም በግልጥ ቃል፦ “ዘፊን፤ ኖት፤ (ዘፈን ይዘፍን ይዝፍን፡፡ ዐረብ)፤ መዝፈን መወዛወዝ፤ ማሸብሸብ ማጋፈት መዝለል መፈንጨት፡፡ … ዘፋኒ፤ (ኒት፤ ንያን፤ ያት)፤ የሚዘፍን ዘፋኝ፤ ተወዛዋዥ፡፡ ዘፈን፤(ናት)፤ በቁሙ ዝላይ እስክታ፡፡”[2]
    የደስታ ክለ ወልድ መዝገበ ቃላትም “ዘፈን”[3] የሚለውን፣ “ዘፈን፤ (ዘፊን ዘፈነ)፤ ቀነቀነ አወረደ ግጥም ገጠመ፣ አዜመ፣ አንጐራጐረ፣ ዘለለ፣ ተውረገረገ፡፡” አሁንም ዘፈነ፤ ተንቀጠቀጠ ተንዘፈዘፈ፡፡ ዘፋኝ(ኞች)፤ የዘፈነ የሚዘፍን፤ አውራጅ አንጐራጓሪ ዘፈን ወዳድ(መዝ.፹፯፥፯)” በማለት ሲያስቀምጡት፣ ገላ.5፥21 ላይ የተቀመጠውን ዘፋኝነት የሚለውን ሃሳብ ደግሞ፣ “መጽሐፍ ግን መሶልሶል[4][ሶለሶለ - አንሶለሶለ፣ አዞር፣ አንቀዠቀዠ፣ አንቀለቀለ መንሶልሶል፣ መዞር፣ መንቀዥቀዥ] ይላል” በማለት ጥቅሱን ጠቅሰው አስቀምጠውታል፡፡
   ሰርጸ፣ ሽምጥጥ አድርጎ “የመጽሐፍ ቅዱስ መተርጉማን ሌላ ስያሜ ስላጡለት ዘፈን አሉ እንጂ ዘፈን መባል አይገባውም” የሚል ጽኑ አቋሙን ደጋግሞ አስተጋብቷል፡፡ ምናልባት ይህንን ሲል ሁሉን አዋቂ ነገር ጠንቃቂ ወደመሆን የተጠጋ ሳይመስለው፤ እንደሆነ ሳያስብ አልቀረም፡፡ ነገር ግን የእርሱን ሃሳብ መተርጉማኑም ሆኑ የቋንቋው ሊቃውንት ሲደግፉት ፈጽሞ አይታይም፡፡

Wednesday, 14 June 2017

አታወሳስቡብን!

ውስብስብ አይደለም ያልተብራራ ቅኔ
ለእርሱ እንደተገባሁ ኃጢአተኛው እኔ፤
ለብዙ ኃጢአቴ እልፍ ምሕረት ፈሶ

Sunday, 11 June 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ አንድ)

Please read in PDf
የምንዋጋው ከማን ጋር ነው?
    በአጭር ቃል፣ የየራሳችንን ሰባኪና ማኅበር፣ ዘማሪና መጋቢ፣ የሐሰት አጥማቂዎችን፣ የነቢያትና “መፍትሔ አምጪ ነን” ባይ የሆኑ የመጋብያን ትንቢተኞችን  … ቃል ከኢየሱስ ጌታችን ቃል ይልቅ በማድመጥና በመከተል ስተናል፡፡ ልክ እንዲሁ ከማን ጋር እንደምንዋጋ አለማወቃችን ከደካማው ፍጡር ጋር በመታገል ዘመናችንን እንድንጨርሰው አድርጐናል፤ መጽሐፍ ቅዱስ ከማን ጋር እንደምንዋጋ፥ “መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ፤” (ኤፌ.6፥12) በማለት ገልጦታል፡፡

Thursday, 8 June 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥር)

Please read in PDF
5.  ውነተኛ ወታደር በማናቸውም የራሱ እቅድና ዝግጅት ቢኖረውም ዘወትር ግን ወደየትኛውም አቅጣጫ መሄድና ማናቸውንም ሥራዎች ለመሥራት ዝግጁ ነው፡፡ እውነተኛ ክርስቲያንም የራሱ የሆኑና በግሉ የሚሠራቸው ብዙ መልካም ነገሮች ሊኖሩት ይችላሉ፤ ነገር ግን በክርስትና ሕይወት ጉዞው ቀዳሚውና ዋናው የሚኖርለት የክርስቶስ ነገር ሊሆን ይገባዋል፡፡
      ክርስቲያኖች ከክርስቶስ ላነሰ ኑሮ ልንኖር አልተጠራንም፡፡ ክርስቲያን ከእርሱ ላነሰ ኑሮ የሚኖር ከሆነ ከሁሉ ይልቅ ምስኪን ነው፡፡ የክርስቶስ የሆኑቱ ታማኞቹ ደቀ መዛሙርት፣ “በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮች” (ሐዋ.1፥8) የሆኑት፣ ለየትኛውም ለጌታችን ኢየሱስ ሥራ ዝግጁና በማናቸውም አቅጣጫ ቢሄዱ በደስታ በመታዘዝ ነበር፡፡ ለየትኛውም አገልግሎትና ለኢየሱስ ጌታችን ሥራ የጨከነና የበረታ ልብና መንፈስ ነበራቸው፡፡

Saturday, 3 June 2017

ሙሽሪትን ሊያስውብ

ክርስቶስ በሞቱ በደሙ ያቆማትን
ከፊት መጨማደድ ሊያጠራና “ሊያድን”
አዲስ ማኅበረሰብ አዲስ ልዩ ትውልድ

Thursday, 1 June 2017

ዘፈን - የወደቀው መልአክ እንጉርጉሮ (ክፍል 4)

Please read in PDF

የቤተ ክርስቲያን አባቶችም ዘፈንን በኀጢአትነቱ ገልጠዋል፤

   የቤተ ክርስቲያን አባቶች ስንል እንዲሁ ከምንም ነገር ተነስተን አይደለም፡፡ እኒህ አባቶች ለእውነተኛው የክርስትና ትምህርት በመጽሐፍ ቅዱስ እውነት ላይ ቆመው ዋጋ የከፈሉ በመሆናቸውና ለመጽሐፍ ቅዱስ እውነት “በመሟገታቸው” ነው፡፡ ትምህርቶቻቸው፣ ምክሮቻቸው፣ ተግሳጾቻቸው ብቻ ያይደለ የሕይወታቸውም ቅድስና ጭምር የተመሰከረላቸው፣ የእግዚአብሔርን ሉዓላዊነትና የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣን አምነው የተቀበሉና በዚህም መሠረትነት ላይ ቆመው የጻፉ መሆናቸውን በመመዘን የምንቀበላቸው ናቸው፡፡
   ከእነዚሀ ቅዱሳን አባቶች መካከል ዘፈንን በግልጥ የተቃወመውና እንድንርቀው ያስተማረን አባት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ነው፡፡  ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በተግሳጹ እንዲህ አለ፣ “ስለዚህ … ዘፈንን ትተዉ ዘንድ እማልዳችኋለሁ፡፡ ኀላፊ የሚሆን ፈቃደ ሥጋን ተዉት ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡ ሲዘፍኑ ላደሩት ጧት ለዋሉት ማታ መሸታ መግዛትን ተው ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡”[1] “ዳግመኛም ሲሰስን እንዳየኸው ጋሬዳ፤ ዘፈን፤ ጨዋታ፤ መሸታ ወዳለበት ሲሔድ ብታየው፡፡ ይህንንም ይተው ዘንድ መላልሰህ ማልደው፡፡”[2]

Wednesday, 24 May 2017

አርጓል በክብር

መቃብሩን በድንጋይ በማኅተም ቢያትሙ
አልተነሣም ብለው በገንዘብ ቢስማሙ

Tuesday, 23 May 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል ዘጠኝ)

Please read in PDF
3.     ከራን ተቀባይ ነው“እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎ ወታደር ሆነህ፥ አብረኸኝ መከራ ተቀበል” (2ጢሞ.2፥3)፡፡ የእውነተኛ አማኝም ሆነ አገልጋይ ዋና መገለጫው፣ ከጠላት ዘንድ የሚመጣበት ብርቱ ሰልፍና ዋና ተቃውሞ ነው፡፡ ክርስቲያንን ከዓለም ጋር የሚያስማማው ምንም የሕይወት ዘይቤ ወይም ሥርዓት የለውም፡፡ ጌታ ራሱም፣ “በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ” (ዮሐ.16፥32) በማለት መከራው የማይቀርና ነገር ግን አሸናፊው ቀድሞ መከራውን ስላሸነፈው ፍርሃት እንደማይገባ አስረግጦ ነግሮናል፡፡ ዓለም ስለእኛ የምትመሰክረው “በጎ ነገር” ካላት፣ ክርስትናችንን ቆም ብለን መፈተሽ ይገባናል፡፡
    ቅዱስ ጢሞቴዎስ በኋለኛው ዘመኑ በመከራው ጽናትና እየሆነ ባለው ነገር ፈጽሞ በፍርሃት ተውጦ ነበር፡፡ ስለዚህም ከመከራው ጽናት የተነሣ መንፈሳዊ ድፍረትን አጥቶ ነበር፤ (2ጢሞ.1፥7)፡፡  በመፍራትም ወደኋላ እንዳይል አበክሮ ቅዱስ ጳውሎስ ያበረታታዋል፡፡ እምነታችንም፤ አገልግሎታችንም በክርስቶስ ጸጋ ላይ የተመሠረተ ነው፤ ደግሞም ይህን ብርቱ ሥራ መከራ በመቀበል ልናምነውና ልናገለግለው ይገባናል፡፡ ውጊያችንም ሁሉ ታላቅ ወታደራዊ ጽናትን በሚጠይቅ ማንነት ውስጥ ማለፍ ይገባናል፡፡