Wednesday, 12 April 2017

ሰሙነ ሕማማት - “ … ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና” (1ቆሮ.11፥26)

 የጌታ ጾም መታሰቢያ የመጨረሻው ሳምንት ስያሜ ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ በዚህ ሳምንት ከምን ጊዜውም በላይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአይሁድ “ወገኖቹ” የደረሰበት ጸዋተወ መከራ ከወንጌላት፣ ከግብረ ሕማማትና ከሌሎችም መጻሕፍት እየተውጣጡ ይነበባሉ፤ ሕማማቱንም ማዕከል ያደረጉ ሥርዓተ አምልኮዎች በጸሎት፣ በዝማሬ፣ በንባብና በቅዳሴ ይቀርባሉ፡፡
   ቅዱስ ጳውሎስ የጌታን ሕማም የጌታ እራት በቀረበበት ጊዜ መናገርና መመስከር እንዳለብን “ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ሁሉ፥ ይህንም ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና፤” (1ቆሮ.11፥26) በማለት ይናገራል፡፡ ጌታ ኢየሱስም ከሙታን መካከል ከተነሣ በኋላ ደቀ መዛሙርቱን፣ “እርሱም፦ ከእናንተ ጋር ሳለሁ በሙሴ ሕግና በነቢያት በመዝሙራትም ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል ብዬ የነገርኋችሁ ቃሌ ይህ ነው አላቸው፡፡ በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤ እንዲህም አላቸው፦ ክርስቶስ መከራ ይቀበላል በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ይነሣል፥” (ሉቃ.24፥46) አላቸው፡፡

Saturday, 8 April 2017

“Wanti kun ija kee duraa dhokatee jira” (Luqa.19:12)

Please read in pdf   

 Torbeen kun Moggaafama “Hosaa’inaa” jedhu qaba. Moggaasa kana Qulqulluun Yaareed torbeewwan sooma Kristoos hunda moggaaseen kan moggaafamee dha. Yaareed torbeewwan sooma guddaa kana keessa jiran hunda baruumsa Kristoos wajiin walsimsiidhaan moggaasa kenneefi jira. Kanaanis Kristoos bu’ura waan hundaa ta’u isaa agarsiisee jira.
    Hosaa’inaan seenaa mataa isaa danda’e qaba. Nuti garuu seenaa balla’a keessa kutaa seensaa qofa ilaala. Goftaan Yasuus “gaara Ejersaa” irraa bu’e gara magaalaa Yerusaalemitti gale. Gaara ejersaa irra taa’e magaala Yeruusaaleem gutumaan guututti arguu ni danda’a ture. Haata’uti gaara irraa bu’e gara magaalatitti seene. Lubootni, barsiisootni fi hoggantootni Ayihuud gara hammenyaan akka isa morman osoo beeku(Maar.15:12); dabalataaniis yeroo dhiyoo keessatti magaalatti fi ummata irratti naasuu fi badiin guddaan akka irratti qaqqabuu beekuu gara magaalaatti seene.

Sunday, 2 April 2017

ኒቆዲሞስ - ለሕጉ እውነት የሚሟገት ጻድቅ! (ዮሐ.7፥51)

Please read in PDF

“ሕጋችን አስቀድሞ ከእርሱ ሳይሰማ ምንስ እንዳደረገ ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን?”
    ነቢያት ለሕጉ ቀናተኞችና ሕጉ እንዲተገበር የሚተጉ ከእግዚአብሔር ለሕዝቡ የተላኩ ናቸው፡፡ ከእግዚአብሔር የተነገራቸውንና በተለያየ መንገድ የተቀበሉትን (ዕብ.1፥1)፤ በማናቸውም ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ሆነው የሚታዘዙትን (ኤር.1፥7) የትንቢት ቃል ሸክም ከእግዚአብሔር በተላኩ ጊዜ (ኤር.1፥4 ፤ ሉቃ.3፥2) ሳይሸራርፉ፤ ሳይቀንሱና ሳይጨምሩ እንዲናገሩ ይገደዳሉ፡፡ በዋናነት ነቢያት ራሳውና ሕዝቡ እንደሕጉ እንዲኖሩ ትልቅ ሥራን ይሠራሉ፡፡ ደጋግመውም የሕጉን መጽሐፍ ያውጃሉ፡፡ ከዚህ የበለጠ ትልቅና ዋና ሥራም የላቸውም፡፡

  ከዚህም ባሻገር፣ ጌታ እግዚአብሔርም ሕግ ሲላላ ሕዝብ ወደተላላነት እንደሚያደላ አስቀድሞ ስለሚያውቅ መሪዎችና አስተዳዳሪዎችን እንደወደደው ይሾማል፡፡ የአይሁድ መምህራንም የተጠሩበት ዋና ዓላማም ይህ ነበር፤ የሕዝቡ መሪና የሕግ መምህራን እንደመሆናቸው መጠን ሕጉን በመጠበቅ ለሕዝቡ ትልቅ ምሳሌ በመሆን፣ ሕዝቡን ያስተምራሉ፤ እንዲጠብቁም ያደርጋሉ፡፡ ዳሩ፣ በአንድ ወቅት በሕዝቡ መሪዎችና በሕጉ መምህራን መካከል ጌታ ኢየሱስን በተመለከተ ትልቅ ክርክር ሆነ፡፡ ለሕዝቡ ጥቂቱን እንጀራና ዓሳ ለብዙ ሺሆች በመመገቡ ምክንያት፣ ከመከበርና ከመደነቅ ይልቅ ለመገደል በቂ ምክንያት ሆነ፡፡

Tuesday, 28 March 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል ሰባት)

                                                         Please read in PDF

7.   አገልጋይ ለጌታው በፍጹም ፈቃዱና በፍጹም ሃሳቡ መታዘዝ ይገባዋል፦ ከሕጉ ትዕዛዛት አንዱ “ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ” (ዘጸ.20፥3) የሚል ነው፤ ይህ ቃል የምሥራቅ ዓለሙን ሁሉ አምላኪነት የሚቃወም ብቻ ሳይሆን፣ እስራኤል እግዚአብሔርን በመፍራትና በማክበር ልታመልከው እንደሚገባ ፍጹም አመልካች ሕግ ነው፡፡ ይህ ቃል በአዲስ ኪዳን ሌሎችንም ሃሳቦች በውስጡ ይዟል፡፡ ይኸውም (1) አማኞች ቅዱስ ለሆነው እግዚአብሔር ከአማልክትና ከርኩሳን አጋንንት ራሳቸውን በመለየት መቀደስ አለባቸው፡፡ ከከንቱ አማልክትም መራቅ ይገባቸዋል፡፡ ይህ የቆሙትንና የሚሰገድላቸውን አማልክት ብቻ ይይደለ፣ ከእግዚአብሔር ያስበለጥነውን ወይም ያስተካከልነውን ማናቸውንም ነገራችንን ይመለከታል፡፡ (2) አማኞች እግዚአብሔር በጎውን ነገር ብቻ እንደሚሰጣቸው  በማመን በፍጹም ኃይላቸውና ፈቃዳቸው፤ ሃሳባቸውም ሊያምኑትና ሊታዘዙለት ይገባል፤ (ዘዳግ.6፥5 ፤ ፊልጵ.3፥8)፡፡

Sunday, 19 March 2017

“እነሆ፥ አስቀድሜ ነገርኋችሁ” (ማቴ.24፥25)

                                          Please read in PDF

   ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር ሳለ ከተናገራቸው የመጨረሻ ቃሎች መካከል፣ በደብረ ዘይት ለደቀ መዛሙርቱ ስለዳግመኛ መምጣቱ ምልክቶች የተናገረው አንዱና ሠፊውን ክፍል የያዘ ነው፡፡ በውስጡ ብዙ ነገር መናገሩን ወንጌላዊው ጽፎልናል፡፡ በመካከሉም ቅዱስ ማቴዎስ፣ ጌታችን “እነሆ፥ አስቀድሜ ነገርኋችሁ” ብሎ መናገሩን ከጻፈልን የወንጌል ቃል ውስጥ ሁለት መሠረታዊ ጭብጦችን ማውጣት እንችላለን፤ ይኸውም፦
1.      ጌታችን ሁሉንም ነገር የነገረን  በግልጥ ነው፦ ጌታ ለእኛ ከሚያስፈልገን  ቀድሞ ያልተናገረን ምንም ነገር የለም፡፡ በሰማይም ሆነ በምድር ሊሆንና ሊመጣ ያለው ነገር ሁሉ ተነግሮናል፡፡ በዚህ ምድር ሕይወት ስላለው ብርቱ ሰልፍነት፣ ታ ኢየሱስንም አምነን በመከተላችንም ሆነ ሳናምን በመከተላችን ስለሚገጥመን ሕይወትና ሞት፣ ስሙን አምነን በመከተላችንና በመመስከራችን ስለሚያገኘን ነቀፋ፣ ስድብ፣ ግርፋት፣ ስደት፣ ስም ማጥፋት፣ ርስትና ጉልት ማጣት፣ በቤተሰብ ሁሉ ዘንድ ከበሬታና ቦታ መነፈግ፣ መጠላትና መገለል፣ መገደል፣  ... እኒህ ሁሉ አስቀድመው የተነገሩ ናቸው፤ (ማቴ.10፥16 ፤ 24፥9 ፤ ዮሐ.15፥19)፡፡

Monday, 13 March 2017

አትተወን

የትዳር አልጋችን ረከሰ ከየሰ
የኪዳን ቃላችን ሳይውል ፈራረሰ
ከባልንጀራ ጋር በሐሜት ተራኩተን
አንድ ነን እያልን አለቅን ተበላልተን፡፡

Wednesday, 8 March 2017

“የረዳኝን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ”

  
    ልክ ዛሬ፣ የዲያቆን አቤንኤዘር ተክሉ ገጽ በሚለው የጡመራ መድረክና(Blog) በፊት ገጽ(Facebook) መጻፍ ከጀመርኩ አራት ዓመታትን አስቆጠርኩ፤ በእነዚህ ዓመታት ውስጥ በጌታ ጉልበትና ቸርነት፤ በመንፈስ ቅዱስም እርዳታ ሃሳብን በማስፈር ቀስ ብዬ እየዳኽኩ፤  እያደግሁ መጥቻለሁ፤ ገና ወደፊትም ጌታ እንደረዳኝ ብዙ እንደምሠራ መሻቴ ነው፤ ግና ጌታ ብቻ እንደፈቀደ ይሁን፤ አሜን፡፡ ምኞቴና መሻቴ አንዱንና የሞተልኝን ጌታ ኢየሱስን በዘመኔ ሁሉ አክብሬ ማገልገልና ማረፍ ነው፤ ለእርሱ ኖሮ መሞት መታደል፤ እጅግ ወደር የለሽ ክብር ነው!

Sunday, 5 March 2017

ምኩራቡን ለምኩራቡ ጌታ አገልግሎት!

    
Please read in PDf
  የእስራኤል ልጆች በስደት ምድር በባቢሎን ሳሉ፣ በኢየሩሳሌም የነበረው ዋናው ቤተ መቅደስ  ስለፈረሰና በምርኮ ምድር ደግሞ ቤተ መቅደስ መሥራት ስላልተቻላቸው ለጸሎት፣ ቃሉን ለማንበብና ለማጥናት እንዲሁም መንፈሳዊ ሕይወታቸውን ለማሳደግ ምኩራብን በየአቅራቢያቸው ሠሩ፡፡ በምኩራቡ ውስጥም በየቀኑ የሚነበቡ የተለያዩ የሕግና የነቢያት የብራና ጥቅልሎች ቅዱሳት መጻሕፍት ቅጂዎችን አስቀመጡ፡፡
   የእግዚአብሔር እውነተኛ ሕዝብ በየትኛውም ሥፍራና ሁኔታ ሊያስቀድመውና ሊጠነቀቅለት የሚገባው ነገር ከአምላኩ ጋር ያለው ዝምድና፣ ትስስሩና ግንኙነቱ ሊሆን ይገባዋል፡፡ ይህ ግንኙነት ሊያሳስበው፤ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው በምቹና የተደላደለ ትርፍ ሰዓት ባለው ጊዜ ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁን በስደት፤ ፈጽሞ ምንም ዓይነት ዕድል ላይገኝ በሚችልበት መንገዱ፣ የጌታ ነገር ቀዳሚና ትኩረቱን ሳቢ ሊሆን፤ በሕይወቱም ጭምር ሊሰጥለት ይገባል፡፡

Tuesday, 28 February 2017

ቅድስት ሰንበቴ

አልቅበዘበዝም እረኛ እንደሌለው
ከቶ አልጨነቅም ጥጉን እንዳጣ ሰው …

Friday, 24 February 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል ስድስት)

Please read in PDF

5.    ጌታ ኢየሱስ ራሱን እንደአገልጋይ ቆጠረ (ማቴ.20፥28)፤ “እንዲሁ የሰው ልጅም ሊያገለግልና ነፍሱን ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም” በማለት፣ እንደአገልጋይ እንጂ “እንደጌታ” አለመምጣቱን ተናገረ፤ (ማር.10፥45 ፤ ፊል.2፥8)፡፡ ስለዚህም መብቱን ሁሉ ለእኛ ሲል ትቶ፣ ሕይወቱንም ጭምር ሊሰጥ መጣ፤ (ዮሐ.10፥11)፡፡ ኢየሱስ በማገልገሉ እኛ ወደድኅነተ ሥጋ ወነፍስ፣ በሞት ጥላ ሥር በጨለማ ውስጥ የነበርን ሕዝቦች በእርሱ መምጣትና መገለጥ፣ ዝቅ ብሎ እንደባርያ  ማገልገል ወደሚደነቅ ብርሃንና ወደበዛ ሕይወት መጣን፤ አገልጋይ ለራሱ እንደማይኖር ጌታ ኢየሱስም ለአባቱ ትእዛዝና ፈቃድ እንጂ ለራሱ አልኖረም፤ ይህንንም በአንደበቱ፥ “አብም እንዳዘዘኝ፥ እንዲሁ አደርጋለሁ” “እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ በፍቅሩም እንደምኖር ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ” (ዮሐ.14፥31 ፤ 15፥10) ሲል ተናገረ፡፡

Tuesday, 21 February 2017

Friday, 17 February 2017

በችኩል አገልጋይ

Please read in PDf


ስርጓጉጥ ሳይጠራ
መንገዱ ሳይቀና
ኮረብታው ዝቅ ብሎ
ሸለቆው ደልድሎ
ለመረማመጃ ሳይደላ በቅጡ
እሩጫው ወዴት ነው፣ ችኮላው ምንድር ነው፣ ሳያጠባብቁ?

Tuesday, 14 February 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አምስት)

Please read in PDF
3.    ለክርስቶስ አገልጋዮች የሆንነው በፈቃዳችን ነው፤ ደኅንነት በደመወዝ መልክ አይገኝም፤ ደኅንነት ሁል ጊዜ ከጸጋ ጋር ብቻ የተያያዘ ነው፡፡ ደኅንነት የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ፣ በሠራነውም ሥራና ሰዓት አይወሰንም፡፡ ከጸደቅንና ከዳንን ደግሞ (1ቆሮ.6፥11)፣ ስለጸደቅንበትና ስለዳንንበት ነገር የምናውጀው እውነትና የምንመሰክረው ምስክርነት አለን፡፡
    “ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም” (ኤፌ.2፥8-9) እንዲል አሁንም፣ ዘወትር መርሳት የሌለብን ነገር፣ መዳን ጥረትን አይጠይቅም፤ አገልግሎት ግን ስለዳንንበትና እውነት መመስከርና ማወጅን ይጠይቃልና ጥረትን፣ ድካምን፣ የወዝ ጥሪትን፣ መውጣት መውረዳችንን ይሻል፡፡ የምንለፋው ትሁታን አገልጋዮች ሆነን ነው፤ ዋጋችን በእርሱ እንጂ በሰው ወይም በሌላ አካል ፈጽሞ አይደለም፡፡ ስለዚህም በፈቃድ አገልጋይ ከሆንለት ጌታ እንጂ ዋጋችንን ከማንም አንቀበልም፡፡ ጌታ አገልጋዮቹን የጠራቸው በፈቃዳቸው ነው፤ “ተከተለኝ” በሚል አጭርና ግልጥ ጥሪ፡፡ ለ“ልዩ ሥራ” ካልሆነ በቀር ጌታ ማንንም አስገድዶ ጠርቶ አያውቅም፡፡ ሁሉን በፈቃዱ ስለሚጠራ የሚከፍለውንም ዋጋንም በተመለከተ፣ እንደወደደ መክፈል እንደሚችል በግልጥ ተናግሯል፤ (ማቴ.20፥11-15)፡፡

Thursday, 9 February 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አራት)

Please read in PDF
2. ራተኛ(አገልጋይ) ባሪያ “ባሪያ ተገዥ፤ አገልጋይ ሰው የተማረከ ወይም የተገዛ ግዝ፤ ውላጅ፡፡ …” [1] በማለት ይተረጉሙታል አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፡፡ “ነጻነትና መብት የሌለው፥ በራሱ ፈቃድ የፈለገውን ማድረግ የማይችል፡፡ በመጀመርያ እግዚአብሔር አንዱን ለሌላው ባሪያ እንዲሆን አድርጎ አልፈጠረም፡፡ ቃሉ ለመጀመርያ ጊዜ በስካር ኃጢአት ከወደቀው ከኖኅ አንደበት ተገኘ፤ ዘፍ.9፥26፡፡” [2]
   ቃሉ በመርገም መልክ ለካም ልጅ ለከነዓን የተነገረ ነው፤ እርግማኑ ከባድ ከመሆኑም ባሻገር እግዚአብሔርን የማይወዱ[ለፈቃዱ የማይታዘዙ] ሁሉ የሚደርስባቸው እርግማን ነው፡፡ የራስን ወላጅ ሆነ የዘመድን ኃፍረተ ሥጋ መመልከት አጸያፊና ነውር ነውና፤ (ዘሌ.18፥4-17) ይህን ያደረገው ከነዓን የባርነቱም እርግማን በትክክል ደርሶበት አይቶታል፤ (ኢያ.16፥10)፡፡ ከዚህ በኋላ በባርነት መያዝና በዚያ መኖር የኃጢአት ውጤት አንዱ መገለጫ ሆኗል፡፡ ለዚህም የእስራኤል ልጆች በመሳፍንት ዘመን በአረማውን እጅ በተደጋጋሚ መውደቃቸውንና በባቢሎንም መማረካቸው በቂ ምስክር ሆኖ በመጽሐፈ መሳፍንት ተጽፎ አለ፡፡

Sunday, 5 February 2017

ጌታ ኢየሱስ ለምን ተጠመቀ? (የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF
4.   ድቅን ሁሉ ለመፈጸም   ጽድቅ የሚለው ቃል፣ ቀጥታ ከዕብራይስጥ የተቀዳ ሲሆን ትርጉሙ፥ ፍጹም ትክክለኛነት፣ ቀጥተኛ፣ ፍትሓዊ፣ በጐ ምግባር ማለት ነው፡፡  ይኸውም ከእግዚአብሔር ጋር ባለው ግንኙነት “በትክክለኛ ሁኔታ” ላይ ሆኖ መገኘት ማለትን በግልጥ ያሳያል፡፡ እግዚአብሔር ከመጀመርያው ለሰው ያለው ሃሳቡ እንዲህ ነበር፡፡ ፍጹም ጻድቅና መልካም እንዲሆን፥ ሰው ግን በእግዚአብሔር ፊት በመልኩና በአምሳሉ ሊገኝ አልቻለም፡፡ ወደገዛ መንገዱም በማዘንበል በምሳሌው እንደ መልኩ ማንነቱን በመያዝ (ዘፍ.5፥3) በኃጢአት ተሰነካክሎ ወደቀ፤ ከትክክለኛነትም ተሰናከለና በዕድፈት ረከሰ፡፡
    መጥምቁ ዮሐንስ አስቀድሞ ጌታ ኢየሱስን ለማጥመቅ ፈቃደኛ አልነበረም፤ ምክንያቱም ጌታ ኢየሱስ ምንም በደልና ኃጢአት የሌለበት ፍጹም ጻድቅ መሆኑን አስተውሏልና፡፡ ስለዚህም አብረውት ስለኃጢአታቸው ሊጠመቁ ከቆሙት እንደአንዱ ሊቆጥረው አልደፈረም፤ ይልቁንም ጌታ ኢየሱስ ከሁሉ የተለየ ልዩ መሆኑን የአዋጅ ነጋሪው ሰው ተገነዘበ፡፡ “እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን?” በማለት፣ ራሱን ከኢየሱስ ጋር በማስተያየት፣ ዮሐንስ ራሱ መጠመቅ የሚያስፈልገው ፍጹም ኃጢአተኛ መሆኑን መሰከረ፡፡ በእርግጥም፣ ሰው ከሆነው ከኢየሱስ በቀር አንዳች ፍጹምና ጻድቅ ከምድር ስለጠፋ ክርስቶስ ጽድቃችን ሊሆን መጣ፡፡ እርሱ አንዳች በደልና ነውር ያልተገኘበት ነውና ጽድቅን  በመሥራት ለእግዚአብሔር አቀረበን፤ (ዕብ.4፥14 ፤ 1ጴጥ.2፥22-23)፡፡