Thursday, 9 July 2015

ሐዲስ ሕይወት



                                                 Please read in PDF



ምንጭ ፦ ቴዎፍሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘኢትዮጲያ መልእክት ፤ ፩ኛ አመት የፓትርያርክነት በዓለ ሢመት መጽሔት ፤ ግንቦት ፩ ቀን ፲፱፻፷፬ ዓ.ም ፤ ገጽ ፯- ፱፡፡

     ሰላም ለክሙ ወጸጋ እግዚአብሔር አቡነ ወእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘአፍቀረነ ወሐደሰ ለነ ፍኖተ ሕይወት በመንጦላዕተ ሥጋሁ ከመ ናንሶሱ ውስተ ሐዲስ ሕይወት ወወሀበነ ፍሥሐ ዘለዓለም ዘሎቱ ክብር ወስብሐት ለዓለም ዓለም፡፡
     የሰው ልጅ ዳግም ልደት ያገኘበት መንፈሱ ፤ ሕሊናው ፤ ሁለንተናው የታደሰበት ሁል ጊዜ በየቀኑ የሚታደስበት የዘለዓለም ፍሥሐ መገኛ የሚሆን የእግዚአብሔር ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን፡፡

      ይህን የሐዋርያውን መልእክት መሠረት በማድረግ የእግዚአብሔር ረቂቅ ጥበብ በየጊዜው ያስነሣቸው አበው ሊቃውንት እየተመራመሩ ያደራጁትን የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በዘመናችን የቃልና የጽሁፍ ማሰራጫ ዘዴዎች አማካይነት በአዲስ መልክና አቀራረብ ተርጉመን ለማቅረብ ግዴታችንም ምኞታችንም ስለሆነ በልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ግንቦት  ፩ ቀን ፲፱፻፷፫ ዓ.ም የኢትዮጲያ ፓትርያርክ በኢትዮጲያ ምድር ከተሾመበት ጀምሮ በየጊዜው የሚታተም አንድ መጽሔት መሥርተናል፡፡ ስሙንም “ሐዲስ ሕይወት” ብለነዋል፡፡ ይህም ከላይ የጠቀስነውን የሐዋርያውን ቃል መሠረት በማድረግ ነው፡፡

Sunday, 5 July 2015

ክርስቶስን “በሚያባብል ቃል” … ለምን?! (ክፍል ሁለት)



                                       Please read in PDF

እኒህም፦
       ክርስቶስን እንደሌሎች በሚያባብል ቃል አንሰብክም፡፡
       ሐሰተኝነትንም በማለዘብ አንቃወምም፡፡

ክርስቶስን በሚያባብል ቃል ስላለመስበክ

“እምነታችሁም በእግዚአብሔር ኃይል እንጂ በሰው ጥበብ እንዳይሆን፥ ቃሌም ስብከቴም መንፈስንና ኃይልን በመግለጥ ነበረ እንጂ፥ በሚያባብል በጥበብ ቃል አልነበረም።” (!ቆሮ.2፥4-5)

   ወንጌል ስንሰብክ የሰዎችን ነጻነት (የአመለካከትና የማሰብ) አንጋፋም፡፡ ይህንን ላለመጋፋት ዕውቀትን በጥበብ የመግለጥ መንፈስ ቅዱሳዊ ጸጋን እንጂ (ሐዋ.17፥16-17 ፤ 1ቆሮ.12፥8) የማባበልና የመሸቃቀጥን መንገድ አንከተልም፡፡ የተቆረጠን እውነት ለመናገር በእርግጥም የቆረጠ ልብና መንፈሳዊ ጭካኔ ያስፈልጋል፡፡

Wednesday, 1 July 2015

ዲያስፖራዎቻችንን አናምናቸውም!!!

     
                                       Please read in PDF

     ይህንን ፎቶ ሳይ፥ ደንግጬ ክው ብዬ ነው የቀረሁት!!!  ማን ያምናል ኢትዮጲያውያን “ግብረ ሰዶም በመጽደቁ ደስ ብሏቸው ሰልፍ ወጡ ፤ ወይም እንዲጸድቅላቸው እነርሱም ሰልፍ ወጡ” ቢባል?! ግን ይኸው ሆኖ አየን፡፡

   

Sunday, 28 June 2015

ስለግብረ ሰዶማዊነት ከአየርላንድ ስህተት ምን እንማራለን?

     
                            Please raed in PDF                        

   ጌታ እግዚአብሔር የእስራኤል ልጆች ከግብጽ በወጡ ጊዜ እርሱን በማክበርና በመፍራት እንዲያመልኩት በዓላትን ሰጥቷቸዋል፡፡ ከተሰጡት በዓላት መካከል ደግሞ የፋሲካ ፣ የመከርና የዳስ በዓላት የትኛውም እስራኤላዊ ከሚኖርበት ከስደት ምድሩ በመምጣት በእስራኤል ምድር ተገኝተው እንዲያከብሩ አዟቸዋል፡፡ (ዘጸ.23፥14፥17) በእነዚህ የበዓል ወራት የእስራኤል ጎዳናዎች ሁሉ የሚሸቱት እጅግ የተወደደውን የመንፈሳዊነትን ለዛና ዝማሬ ነው፡፡
      ከጥቂት ዓመታት በፊት በካቶሊክና በፕሮቴስታንት ጎራ ክርስትናዋን ከፍላ ጎዳናዎቿን በደም ያጨየቀችው አየርላንድ ፤ አሁን በጎዳናዎቿ የተሰማው ነውር ጆሮን ጭው የሚያደርግ ነው፡፡ ግብረ ሰዶምን በወንጀል ህጓ ጠቅሳ በመከላከልና ለጋብቻ ባላት እሴቷ በአገራችን ካለው ሕግና እሴት ጋር እጅግ የተቀራረበ ነበር፡፡ አየርላንድ በወንጀል ህጓ በግልጥ ግብረ ሰዶምን መከልከል ብቻ ሳይሆን ፈጽመው የተገኙትንም ትቀጣ ነበር፡፡

Sunday, 21 June 2015

ክርስቶስን “በሚያባብል ቃል” … ለምን?! (ክፍል አንድ)

    
                                               Please read in PDF

    ጌታ እግዚአብሔር የነጻነት አምላክ ነው ፤ የወደድነውን ፣ ሕሊናችን የመረጠውን ኃላፊነትን ከሚያስከትለው ውጤት ጋር የመቀበል ሙሉ ነጻነትን ሰጥቶናል፡፡ መንገዳችንን እንደእስራኤል ዘሥጋ ቀድመን ማጥራትና መምረጥ ከእኛ ነው የሚጠበቀው፡፡ መንገዶቹም በረከትና መርገም የሚባሉ እንጂ  ሌላ ሦስተኛ አማራጭ የለም፡፡ ይህንን እውነት ነቢዩ ቅዱስ ሙሴ ምድረ ርስትን ሊወርስ ላለው ፥ ለአዲሱ ትውልድ ሕጉን ለማስተማር ፤ የምክርንም ቃል በተናገረበት አንቀጹ እንዲህ ብሏል፦
“እነሆ፥ እኔ ዛሬ በፊታችሁ በረከትንና መርገምን አኖራለሁ፤ በረከትም፥ እኔ ዛሬ ለእናንተ የማዝዘውን የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ብትሰሙ ፣ መርገምም፥ የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ባትሰሙ፥ ዛሬም ካዘዝኋችሁ መንገድ ፈቀቅ ብትሉ፥ ሌሎችንም የማታውቋቸውን አማልክት ብትከተሉ ነው፡፡” (ዘዳግ.11፥26-29)

Tuesday, 16 June 2015

በክስ አታዳክሙኝ!


                    Please read in PDF  

ለምን እክዳለሁ ፣ አመንዝራነቴን ፤
ሌባና አመጸኛ ፣ ስግብግብነቴን ፤
አላስተባብልም ፣ ስሁት ሰው መሆኔን … ፤

Wednesday, 10 June 2015

ቅዱስ ሲኖዶስና የመሰብሰቡ ዓላማ (የመጨረሻ ክፍል)



3. በግፍና ያለሥራው የሚወገዝ እንዳይኖር ለመከላከል

      “ … ወደጌታችን ወደኢየሱስ ክርስቶስ በፍጹም ንጽሕና በሚቀርቡ ገንዘብ፡፡ ከካህናት ወገን ወይም ከሕዝቡ ወገን ቢሆን ኤጲስ ቆጶስ አውግዞ የለየውን ሰው ፍርድ ይመረምሩ ቸልታ እንዳይሆን ወይም ይህን በሚመስል ነገር ሁሉ እንደተገለጠላቸው ይፈርዱ ዘንድ፡፡” የሚለው የፍትሐ ነገሥቱ አንቀጽ አድሎዐዊነት እንዳይከሰት በውስጡ ማሳሰቢያ አዘል መልዕክት አለው፡፡ የቱም ጤናማ አባወራ ወይም የቷም ጤናማ እማወራ ልጆቿም የምታሳድገው ባለማበላለጥ በእኩልነት ነው፡፡ ኤጲስ ቆጶስም አማኞችን ሲመራ ልክ ቤተሰቡን እንደሚመራው አይነት ምንም አድሎ በማይኖርበት መልኩ ሊሆን ይገባዋል፡፡ (1ጢሞ.3፥4)

Thursday, 4 June 2015

ጰራቅሊጦስ- መንፈስ ቅዱስ


                             Please Read in PDF


  ከግሪኩ “ፓራክሊቶስ” ወይም ከዕብራይስጡ “ፕራቅሊጥ” ከሚለው ግስ የተገኘው “ጰራቅሊጦስ” የሚለው ቃል ትርጉሙ “ አማላጅ ፣ አስታራቂ ፣ አፍ ፣ ጠበቃ ፣ ትርጁማን ፣ አምጃር ፣ እያጣፈጠ የሚናገር ፣ ስብቅል ካፉ ማር ጠብ የሚል፡፡ … ፤ ናዛዚ ፣ መጽንዒ ፣ መስተፈስሒ ፤ መንፈስ ቅዱስ፡፡” በማለት አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ተርጉመውታል፡፡ (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ/አለቃ/፤ መጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ፡፡(1948 ዓ.ም)፤አርቲስቲክ ማተሚያ ቤት፡፡ ገጽ.907)

Sunday, 31 May 2015

ለመኪና ሸላሚዎችና ተሸላሚዎች “አማኞች” ምክር ቢሆን!



    “የሚያበራየውን በሬ አፉን አትሰር” (ዘዳ.25፥4 ፤ 1ቆሮ.9፥9)

  ቅዱስ ነቢይ ሙሴ፥ እስራኤል የሚገለገሉባቸውን እንሰሳት በተለይም በሬ እያበራየ ባለበት ወቅት ጤንነቱ እንዲጠበቅ በቂ ምግብ ማግኘት እንዳለበት ሕዝቡን ያዛል፡፡ ይህም በመራራት ፣ የሚሰጡትን አገልግሎት በማሰብ እንሰሳቱን መንከባከብ ፣ ተመጣጣኝና የሚበቃቸውን ያህል መብልን ሊሰጣቸው እንደሚገባ ያሳስባል፡፡ ይህ ለእንሰሳት የተነገረው ቃል ፥ በአዲስ ኪዳን ቃል በቃል ለጌታ ወንጌል አገልጋዮች የአገልግሎት መርሕ ተደርጎ ተወስዷል፡፡

Friday, 29 May 2015

ቅዱስ ሲኖዶስና የመሰብሰቡ ዓላማ (ክፍል - 2)

     

                                                                    Please read in PDF      

 
  “በበጋና በበልግ ወራት ቸነፈር የድንገት ሞት ይበዛልና ከሞት አስቀድሞ ፍቅር ሰላም ይሆን ዘንድ፡፡” እንዲል  “ … ለእርሱ ስለ ሆኑት ይልቁንም ስለ ቤተ ሰዎቹ የማያስብ ማንም ቢሆን፥ ሃይማኖትን የካደ ከማያምንም ሰው ይልቅ የሚከፋ ነው።” (1ጢሞ.5፥8) በሚራራና በፍቅር ስስት ለሃይማኖት ቤተሰብ ማሰብ ከአማኝ ሁሉ የሚጠበቅ መንፈሳዊ ግዴታ ነው፡፡ ከአንደኛው ሃሳብ ጋር ብናስተሳስረው የአምልኮዓችን ጤንነት ያለው ለባልንጀራችን ባለን የርኅራኄ ዕይታ ነው፡፡ ባልንጀራችን ለአደጋ ተጋልጦ (ሉቃ.10፥29-37) ፣ ተርቦ ፣ ተጠምቶ ፣ ታርዞ ፣ ታስሮ (ማቴ.25፥37-40) ፤ በስደትና በመቅበዝበዝ ሲኖር ሳለ እኛ ተቀማጥለን ልብስና ምግብ በማማረጥ ያማሩ ቤቶች ሠርቶ ዕቃዎችን በመገጥገጥ እንድንኖር ክርስቲያናዊ አስተምህሮም ሆነ ትውፊቱ በዝምታ ይነቅፈናል፡፡

Saturday, 23 May 2015

ድል የነሣው ጌታ - አርጓል!



   
  ጌታ ወደሰማያት ያረገው ከአባቱ ዘንድ የተላከበትን ዋናውን ዓላማውን “እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤” (ዮሐ.17፥4 ፤ 13፥31) በማለት ፈጽሞ (ዮሐ.19፥30) ያከናወነ መሆኑን ተናግሯል፡፡ (ዮሐ.19፥30) ጌታችን ከአባቱ ዘንድ የተላከበት ዋና ዓላማው፥ የሰውን ልጅ ከዘላለም ሞትና ቀንበር ማዳን ነው፡፡ (ሉቃ.9፥56 ፤ 19፥10 ፤ ዮሐ.3፥15 ፤ 17 ፤ 8፥15) ይህንን በመስቀል ላይ በሠራው የፍቅር ሥራው ፈጽሞታል፡፡ ድል መንሳቱንና የሰው ልጆችን መዳን መፈጸሙን ስናነሳ ፥ በጌታ የሆነውን ሁለት ነገሮች ማስታወስ ግድ ይለናል፡፡

Monday, 18 May 2015

ቅዱስ ሲኖዶስና የመሰብሰቡ ዓላማ (ክፍል - 1)


“በየቦታው ሁሉ ኤጲስቆጶሳት በያመቱ ሁለት ጊዜ ከጳጳሳቸው ወይም ከሊቀ ጳጳሳቸው ዘንድ ይሰብሰቡ፡፡ መጀመርያ ከጾመ ፵ በፊት ይሁን፡፡ ክፉንና ቁጣን በሚያርቁ ገንዘብ ቁርባናቸውም ለእግዚአብሔር ንጽሕት ክብርት ቅድስት ትሆን ዘንድ፡፡ ሁለተኛውም ከበዓለ መስቀል በኋላ በመከር ወራት ይሁን፡፡ በበጋና በበልግ ወራት ቸነፈር የድንገት ሞት ይበዛልና ከሞት አስቀድሞ ፍቅር ሰላም ይሆን ዘንድ፡፡ ወደጌታችን ወደኢየሱስ ክርስቶስ በፍጹም ንጽሕና በሚቀርቡ ገንዘብ፡፡ ከካህናት ወገን ወይም ከሕዝቡ ወገን ቢሆን ኤጲስ ቆጶስ አውግዞ የለየውን ሰው ፍርድ ይመረምሩ ቸልታ እንዳይሆን ወይም ይህን በሚመስል ነገር ሁሉ እንደተገለጠላቸው ይፈርዱ ዘንድ፡፡”
(ፍትሐ ነገሥት አን.5 ቁ.165 ገጽ 61)

Thursday, 14 May 2015

ከሳሽ ዕድፉን ሳያይ ...


               Please read in PDF
         

ስታመነዝር አገኘናት፣
ብለው አካልበዋት፣
ከጌታ ፊት እያቻኮሉ፣
ከእግሩ ሥር አምጥተዋት ጣሉ፡፡

Friday, 8 May 2015

“ … ለደቀ መዛሙርቱ እንደገና ተገለጠላቸው” (ዮሐ.21፥1)

  

  ጌታችን ከሙታን መካከል ከመነሳቱ በፊት ገና በተሰቀለ ጊዜ በደቀ መዛሙርቱ ልብ የቀረው ነገር እጅግ አስደንጋጭ ነገር ነበር፡፡ እንዲያውም ተስፋ እስከመቁረጥም አድርሷቸው ሉቃስና ቀለዮጳ ወደመጡባት ከተማ ወደኤማሁስ(ሉቃ.24፥13) ፥ ብዙዎቹም ጥለው እንደሸሹ ያልተመለሱ ሲሆን (ማቴ.26፥56) ፥ ስምዖን ጴጥሮስ ፣ ዲዲሞስ የተባለው ቶማስ ፣ ናትናኤል ፣ የዘብዴዎስ ሁለቱ ልጆች (ያዕቆብና ዮሐንስ) ደግሞ እጅግ ተስፋ ከመቁረጥ የተነሳ የዕለት ጉርሳቸውንና የዓመት ልብሳቸውን ለመሸፈን ጌታ እነርሱን ከጠራበትና ትተውት ተከትለውት ወደነበረው (ማቴ.4፥18 ፤ ዮሐ.21፥1) ወደቀደመ ህይወታቸው አሳ አስጋሪነት(አጥማጅነት) ተመልሰው ተሰማሩ፡፡

Monday, 4 May 2015

ሁለት ብዕርና ምላስ ላላቸው “ሰባኪዎች” ሙግት አለኝ!

     
                                      Please read in PDF            

   ሰሞኑን በISIS ከታረዱት ወገኖቻችን መካከል ኤፍሬም የማነ ስለተባለ ኤርትራዊ ወንድማችን ቀድሞ ሲወራ የነበረው ጀማል በሚል የእልምና ስም እንደሆነና የእምነቱም ተከታይ እንደሆነ ፤ አብሮ ለመሰዋት በመወሰኑ ከክርስቲያን ወንድሞቹ ጋር መታረዱን ብዙ ንግግሮችና ጽሁፎችን አድምጠንም ፤ አንብበንም ነበር፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም ሲነገሩም የነበሩ ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ የሆኑ አስተምህሯዊ ንግግሮች ስናደምጥም ፤ ስናነብም ታዝበናል፡፡ በተጨማሪም ጥቂት የማይባሉ ሰባኪዎች የቤተ ክህነቱንና የቤተ መንግሥቱን የሚድያና የስብከት አውደ ምህረትን ተቆጣጥረው “ጀማል ከክርስቲያን ወንድሞቹ ጋር ሰማዕት ሆነ” በሚለው ዙርያ የተናገሩትንም ሰምተናል ፤ የጻፉትንም አይተናል፡፡ እኒህ ሰባኪዎች ደስ ሲላቸው ራሳቸውን እንደ“ተመራማሪ” ፥ ሲላቸው ደግሞ እንደየ“ፖለቲካ ተንታኝ” ቆጥረው ሳያበቁ “የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ሙላት” እንዳላቸውም ደግሞ ለመስበክ ደፍረው ሲቀርቡም እናያለን፡፡