Friday, 8 May 2015

“ … ለደቀ መዛሙርቱ እንደገና ተገለጠላቸው” (ዮሐ.21፥1)

  

  ጌታችን ከሙታን መካከል ከመነሳቱ በፊት ገና በተሰቀለ ጊዜ በደቀ መዛሙርቱ ልብ የቀረው ነገር እጅግ አስደንጋጭ ነገር ነበር፡፡ እንዲያውም ተስፋ እስከመቁረጥም አድርሷቸው ሉቃስና ቀለዮጳ ወደመጡባት ከተማ ወደኤማሁስ(ሉቃ.24፥13) ፥ ብዙዎቹም ጥለው እንደሸሹ ያልተመለሱ ሲሆን (ማቴ.26፥56) ፥ ስምዖን ጴጥሮስ ፣ ዲዲሞስ የተባለው ቶማስ ፣ ናትናኤል ፣ የዘብዴዎስ ሁለቱ ልጆች (ያዕቆብና ዮሐንስ) ደግሞ እጅግ ተስፋ ከመቁረጥ የተነሳ የዕለት ጉርሳቸውንና የዓመት ልብሳቸውን ለመሸፈን ጌታ እነርሱን ከጠራበትና ትተውት ተከትለውት ወደነበረው (ማቴ.4፥18 ፤ ዮሐ.21፥1) ወደቀደመ ህይወታቸው አሳ አስጋሪነት(አጥማጅነት) ተመልሰው ተሰማሩ፡፡

Monday, 4 May 2015

ሁለት ብዕርና ምላስ ላላቸው “ሰባኪዎች” ሙግት አለኝ!

     
                                      Please read in PDF            

   ሰሞኑን በISIS ከታረዱት ወገኖቻችን መካከል ኤፍሬም የማነ ስለተባለ ኤርትራዊ ወንድማችን ቀድሞ ሲወራ የነበረው ጀማል በሚል የእልምና ስም እንደሆነና የእምነቱም ተከታይ እንደሆነ ፤ አብሮ ለመሰዋት በመወሰኑ ከክርስቲያን ወንድሞቹ ጋር መታረዱን ብዙ ንግግሮችና ጽሁፎችን አድምጠንም ፤ አንብበንም ነበር፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም ሲነገሩም የነበሩ ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ የሆኑ አስተምህሯዊ ንግግሮች ስናደምጥም ፤ ስናነብም ታዝበናል፡፡ በተጨማሪም ጥቂት የማይባሉ ሰባኪዎች የቤተ ክህነቱንና የቤተ መንግሥቱን የሚድያና የስብከት አውደ ምህረትን ተቆጣጥረው “ጀማል ከክርስቲያን ወንድሞቹ ጋር ሰማዕት ሆነ” በሚለው ዙርያ የተናገሩትንም ሰምተናል ፤ የጻፉትንም አይተናል፡፡ እኒህ ሰባኪዎች ደስ ሲላቸው ራሳቸውን እንደ“ተመራማሪ” ፥ ሲላቸው ደግሞ እንደየ“ፖለቲካ ተንታኝ” ቆጥረው ሳያበቁ “የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ሙላት” እንዳላቸውም ደግሞ ለመስበክ ደፍረው ሲቀርቡም እናያለን፡፡

Monday, 27 April 2015

ደማቸው ድምጽ አለው!

                                                   
                                                             Please read in PDF 
                       
   

ከሩቅ የሚሰማ ፣ ከአድማስ ባሻገር፤
ከምድር ዳርቻ ፣ ከቀላያቱ ዳር፤
ሰው ከማይኖርበት ፣ ከዚያ ምድረ በዳ፤
በረሃብና ጥም ፣ ሥጋቸው ቢጎዳ…   

Wednesday, 22 April 2015

“ጌታ ሆይ፥ በISIS ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው”




በድጋሚ በግፈኛው ISIS ለተሰው ክርስቲያን ኤርትራውያን ፣ ኢራቃውያን ቤተሰቦች ጌታ መንፈስ ቅዱስ መጽናናትን እንዲያድላቸው ብርቱ ጸሎታችን ነው!!!
    የአንዲት ሕያው ቤተ ክርስቲያን ልዩና የሁል ጊዜ መገለጫ፥ “የእግዚአብሔርን ቃል ለሁሉ በማዳረስ ማስፋትዋና የደቀ መዛሙርትን ቁጥርና እጅግ የሚታዘዙትንም ማብዛቷ ነው፡፡” (ሐዋ.6፥7) የባለበት ሂድ ወይም የእየቀጨጩ ዕድገት ጤናማነቱ ተፈጥሮዐዊም ፤ መንፈሳዊም አይደለም፡፡ በብዛትም በጥራትም ማደግ የጤናማ ተፈጥሮዐዊና መንፈሳዊ ዕድገት መገለጫ ነው፡፡ ወንጌሉ ሕያው ነውና ተበትኖ ፤ ተሰብኮ እንደዋዛ አይቀርም ፤ ሕያው ፍሬንም ያፈራል እንጂ፡፡
     ክርስትና ገና ጉዞውን በጀመረበት ቀደምት ጊዜያት፥ በአንድ የስብከት ርዕስና በአንድ ብርቱ ተአምራት ስምንት ሺህ የሚጠጉ አማኞች ወደአንድ መቶ ሐያው የጌታ ቤተሰብ ተጨመሩ፡፡ ሥራውን ሠሪው መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ የቁጥሩ አጨማመር ከመደመርም ከብዜትም ይልቃል፡፡ እኛ የቀደምንበት አገልግሎት ጠላትን አለጊዜው ያጎለምሳል ፤ ጌታ የቀደመበት አገልግሎት ግን ጠላት ተኩላ እያለ ሥራውን ያሠራል፡፡(ማቴ.10፥16)

Monday, 20 April 2015

“ISIS” በድርጊቱ እኛን ምን ያስተምረናል?

              
                          Please read in PDF
                             
           

አስቀድመን በድርጊቱ እጅግ ላዘኑ የሟች ቤተ ሰቦችና ክርስቲያኖች ሁሉ የመጽናናትን መንፈስ አጽናኙ መንፈስ ቅዱስ እንዲያድላቸው እንመኛለን፡፡

     አለሙ እጅግ በክፋት እንደተያዘ (1ዮሐ.5፥19) ፤ ክፉዎችም ምድርን ሊያስጨንቋት እንደሚችሉ ታላቁ መጽሐፍ በግልጥ ይነግረናል፡፡ (ማቴ.24፥21) ክፉዎች ምድርን የሚያስጨንቋት በሦስት ብርቱ ምክንያቶች ይመስለኛል ፦
1.     የእግዚአብሔር ሕዝብ ከእግዚአብሔር ሲለይ፤
2.    ህዝቡ መለየቱን ሳያውቅ ንስሐ ሳይገባ ሲቀር ፤
3.    ያመንነው ወንጌል ጠላትን እጅግ ያስጨነቀው እንደሆን፡፡

Saturday, 18 April 2015

እንጭጭ ክርስትና!


                      Please read in PDF       

ጸሎት እወዳለሁ ባ'ምላኬ ፊት መቆም፤
ምጽዋትም ሰጣለሁ ድኀ ለመደጎም፤
አብዝቼ ጾማለሁ ከምግብ ውኃ ርቄ፤

Saturday, 11 April 2015

“የተሰቀለው … ተነስቶአል ፥ በዚህ የለም፤” (ማር.16፥6)



Please read in PDF

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ!!!
     የሙታን ትንሳኤ ትምህርት ክርስትና ከቆመባቸው መሠረታውያን ዶግማውያን ትምህርቶች ከሆኑት አንዱና ዋናው ትምህርት ነው፡፡  (1ቆሮ.15፥13 ፤ ዕብ.6፥2) መናፍቃን ከሚመዘኑበት መመዘኛ አንዱ ለትንሳኤ ሙታን ባላቸው የአስተምህሮ አቋም ነው፡፡ የትኛውም አማኝም ሆነ የእምነት አቋም ትንሳኤ ሙታንን በግማሽም ቢሆን ባጠቃላይ ቢክድ በቀደመው ዘመን ከነበሩት መናፍቃን እንደአንዱ መቆጠሩ ምንም የማያሻማ ነው፡፡ ሐዋርያው ለዚህም ነው ፦ “ትንሣኤ ሙታንስ ከሌለ ክርስቶስ አልተነሣማ ፤ ክርስቶስም ካልተነሣ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት ፤ ደግሞም፦ ክርስቶስን አስነሥቶታል ብለን በእግዚአብሔር ላይ ስለ መሰከርን ሐሰተኞች የእግዚአብሔር ምስክሮች ሆነን ተገኝተናል፤ ሙታን ግን የማይነሡ ከሆነ እርሱን አላስነሣውም።” (1ቆሮ.15፥13-15) በማለት አጽንቶ የተናገረው፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ለዚህ በአንቀጸ ሃይማኖቷ “የሙታንን ትንሳኤ እናምናለን” በማለት በግልጥ የምትመሰክረው፡፡

Wednesday, 8 April 2015

በኢየሱስ ላይ የተሤረ ሤራ (ሉቃ.22፥3-6)

        
                              Please read in PDF


      የተወደደው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕውር ስላበራ ፣ ለምጻም ስላነጻ ፣ አንካሶችን ስላስኬደ ፣ ደንቆሮችን እንዲሰሙ ስላደረገ ፣ ሽባ ስለተረተረ ፣ ጉንድሾችን ስላዳነ ፣ ጎባጣ ስላቃና ፣ ሙታንን ስላስነሳ ፣ አጋንንትን ስላወጣ (ማቴ.9፥25 ፤ 11፥5-6 ፤ 15፥30-31) ፣ በድካም መንፈስ ተይዘው ለሚሰቃዩት ዕረፍትን ስላደለ (ሉቃ.13፥11) ፣ ኃጢአተኞችን ስለተቀበለና ከእነርሱም ጋር ስለበላ (ሉቃ.15፥2)

Sunday, 5 April 2015

ሆሳዕና መባል ይገባዋል!!!



                                                Please read in PDF


       ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአባቱና ለእኛ የታዘዘበትን የገዛ ዘመኑን (1ጢሞ.2፥7) በመፈጸም ወደአባቱ ለመሄድ በመወሰኑ ምክንያት ለመጨረሻ ጊዜ ከኢያሪኮ (ማቴ.20፥29 ፤ ማር.10፥46 ፤  ሉቃ.19፥1) “ወደ ኢየሩሳሌምም ከደብረ ዘይት አጠገብ ወዳሉቱ ወደ ቤተ ፋጌና ወደ ቢታንያ” ሄደ፡፡ ጌታችን ወደኢየሩሳሌም የወጣው አይሁድ እንደሚገድሉት ፤ በእርሱም ላይ እንደተነሳሱ እያወቀ ነው፡፡ (ማቴ.20፥17-19 ፤ ማር.10፥32 ፤ ሉቃ.9፥22 ፤ 44 ፤ 18፥31) ነፍሱን በፈቃዱ ስለበጎቹ ያኖረው ጌታችን (ዮሐ.10፥16) ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ ነው ስለእኛ የሞተው፡፡

Sunday, 29 March 2015

ኒቆዲሞስ - በክፉዎች መካከል የበቀለ መልካም ተክል

                                            
                                       Please read in PDF     
                                               
  


      በቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት፥ ቅዱስ ያሬድ እንደሰየመው አሰያየም ፥ያለንበት ሳምንት “ኒቆዲሞስ” ይባላል፤ ቅዱስ ያሬድ፥ ጌታ ኢየሱስ ነገረ ጥምቀትን ለኒቆዲሞስ እንዳስተማረው በማውሳት “ሆረ ኃቤሁ ዘስሙ ኒቆዲሞስ” ማለትም “ኒቆዲሞስ የሚባለውም ወደእርሱ ሄደ” ብሎ ርዕስ ሰይሞ ዘምሮታልና ፤ ቤተ ክርስቲያንም ይህን በማሰብ የጌታን ፆም አንዱን ሳምንት ሰይማ ፥ ጌታዋን ታመልክበታለች፡፡

Sunday, 22 March 2015

ቸር አገልጋይ ማነው?











“በጎ ሥራ እየሠራ ጌታው የሚያገኘው ቸርና የታመነ አገልጋይ ማነው ? ባለው ሁሉ ላይ የሚሾመው ደግሞም  እግዚአብሔር ቸር ታማኝ አገልጋይ በጥቂቱ የታመንክ ወደጌታህ ደስታ ግባ የሚለው፡፡
(ቅዱስ ያሬድ)

      የስድስተኛውን የዓቢይ ጾም ስያሜ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ “ገብር ኄር” ትርጓሜውም “መልካም ባርያ” ሲለው ፤ የዕለቱን የመዝሙር ርዕስ ደግሞ “መኑ ውእቱ ገብር ኄር” ትርጓሜውም “ቸር አገልጋይ ማነው?” ብሎ ሰይሞታል ፤ የሚነበበው የወንጌል ክፍል ደግሞ  ማቴ.25፥14-31 ነው፡፡ በዚህ ዕለት በዋናነት “ስለቅን አገልጋዮችና ስለአገልግሎታቸው ትጋት “ገብር ኄር” እያለ ዋጋን የሚከፍል ፤ ሰነፍና ታካች አገልጋዮችን የሚቀጣም አምላክ እንዳለ በስፋት ይወሳል፡፡”

Thursday, 19 March 2015

እኔ ላንተ ፈራሁ!


                                  Please read in PDF 


ትመስለኝ ነበረ፣ ለጨለማው ብርሃን ፣ ለጣዕም አልባው ጨው
ትመስለኝ ነበረ፣ ለብ ያለውን ሁሉ ፣ ግለህ ʻምታግለው
ትመስለኝ ነበረ፣ ብርሃንህ የበራ ከእንቅብ በላይ ሆኖ
ትመስለኝ ነበረ፣ ከጨለማ በላይ ከጋኑም ከፍ ብሎ

Sunday, 15 March 2015

ጌታ ሆይ ፤ ና! (1ቆሮ.16፥22)


                                                 Please read in PDF
 

     
 የጥንት ክርስቲያኖች ጌታ ወደሰማያት ከማረጉ ምንም ሳይቆይ በመናፈቅ ለሁልጊዜ ይጮኹ የነበሩት የዳግመኛ መምጣቱን ነገር እንደሆነ ታላቁ መጽሐፍ አስረግጦ ይነግረናል፡፡ የአዲስ ኪዳን የትንቢት መጽሐፍ የሆነው የራዕይ መጽሐፍ የመጽሐፉን መግቢያ ሲጀምር በተደጋጋሚ “ቶሎ ይሆን ዘንድ የሚገባውን ነገር… ” እንደሆነና ጌታ ባረገ ገና አንድ ምዕት ሳይሞላው “ዘመኑ ቀርቦአልና …” (ራዕ.1፥1 ፤ 3) በማለት ዘመኑ በደጅ የቀረበ መሆኑን በግልጥ ተናግሮ ሳያበቃ መጽሐፉን የዘጋው “ዘመኑ ቀርቦአልና … እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ … መንፈሱና ሙሽራይቱም ፦ ና ይላሉ ፦ የሚሰማም ፦ ና ይበል። … አዎን፥ በቶሎ እመጣለሁ ይላል። አሜን፥ ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ና።“ (ራዕ.22፥10 ፤ 12 ፤ 17 ፤ 20) በማለት በተደጋጋመ ናፍቆታዊ መቃተት ነው፡፡

Friday, 13 March 2015

“የምርጫ 97 ቀይ ስህተት እንዳይደገም ”ቤተክርስቲያን ድርሻዋን ብትወጣስ?!


                        Please read in PDF

   
     ቤተ ክርስቲያን አግባብነት ላላቸው የመንግሥት ሕጎችና ሥርዓት ሁሉ ልትገዛ እንደሚገባት ታላቁ መጽሐፍ “ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለ ሥልጣኖች ይገዛ። ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና … ስለ ጌታ ብላችሁ ለሰው ሥርዓት ሁሉ ተገዙ፤ ለንጉሥም ቢሆን፥ ከሁሉ በላይ ነውና … ” (ሮሜ.13፥1 ፤ 1ጴጥ.2፥13) በማለት ያስቀምጣል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ሆነ ቅዱስ ጴጥሮስ ይህንን ቃል የተናገሩት በዚያ ዘመን ምድርን ይገዙ ለነበሩት ሮማውያን ቄሳሮች ፥ ደቀ መዛሙርት እንዲገዙና እንዲታዘዙ በማሳሰብ ነው፡፡ ምክንያቱም ባዕለ ሥልጣናት “ክፉ የሚያደርጉትን ለመቅጣት በጎም የሚያደርጉትን ለማመስገን ከእርሱ (ከእግዚአብሔር) ተልከዋልና … በጎ እያደረጋችሁ፥ የማያውቁትን ሞኞች ዝም ታሰኙ ዘንድ እንዲህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነውና፡፡” (1ጴጥ.2፥14-15)

Tuesday, 10 March 2015

ሰው የለንም ጌታ!


                Please read in PDF

አንቀልባው አረጀ ደከመ አልጋችን
ፈውስህ ራቀንና ቃሬዛ በዛብን
ጎብጦ ሳይል ቀና ኑሮ እንዳከሰለው
ቀኑ እንደጨለመ ይሄዳል ሰው ይኸው፡፡