እግዚአብሔር ጉልበትና ማስተዋል ሆኖኝ ፥ ይኸው ይህን አገልግሎት
ከጀመርኩ ሁለት አመት ሞላኝ፡፡ የዘላለም መዳን ፈቃድን ሲጠይቅ
(ማር.2፥5 ፤ ዮሐ.5፥6 ፤ ሐዋ.8፥37 ፤ 13፥46) አገልግሎት ደግሞ ጥሪና መለየትን ይሻል፡፡ (ዘፍጥ.12፥1-9 ፤ ሐዋ.9፥15)
በየትኛውም ዘመን የተገለገለ የወንጌል አገልግሎት ያለመከራና ነቀፋ ተገልግሎ አያውቅም፡፡ የሐዋርያትን ዘመን ትተን ክርስትና በነጻነት
ተገለገለ የተባለበትን ዘመን ብናይ እንኳ እነቅዱስ አትናቴዎስ ከአርባ አመታት በላይ በከባድ ስደትና ህመም ፤ በስም ማጥፋት ፣
እነቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በእስርና በስም ማጥፋት ክስ የወደዱትን ጌታ አገልግለውታል፡፡
Sunday, 8 March 2015
Wednesday, 4 March 2015
ይገባሃል
ይገባሃል!
|
“ሀያ
አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋን ላይ በተቀመጠው ፊት ወድቀው፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው እየሰገዱ። ጌታችንና አምላካችን
ሆይ፥ አንተ ሁሉን ፈጥረሃልና ስለ ፈቃድህም ሆነዋልና ተፈጥረውማልና ክብር ውዳሴ ኃይልም ልትቀበል ይገባሃል እያሉ በዙፋኑ ፊት
አክሊላቸውን ያኖራሉ።”
(ራዕ.4፥10-11)
|
ይገባሃል ውዳሴ
ይገባሃል ቅዳሴ
ይገባሃል ዕልልታ
ይገባሃል ማኅተሙንም ልትፈታ
ይገባሃል የማያቋርጥ ግርግርታ፡፡
Saturday, 28 February 2015
የጠፉትን ለምን ነው የማንፈልገው?
በኦሮምኛ አንድ የማስታውሰው ተረት አለ ፤ እንዲህ የሚል፦ “Loon
bade loon jiruuf barbaadan” ትርጉም “የጠፋ ከብት
ላለው ከብት ሲባል ይፈለጋል” ፡፡ የተረቱ ጽንሰ ሐሳብ የጠፋውን ከብት የማይፈልግና ፈልጎም የማያገኝ ሰው በበረት ያለውንም ከብት
ይነዱበታል ለማለት ነው፡፡ በእርግጥም የቤት እንሰሳን አጥብቆ አለመፈለግ በደህና በበረት ለሚኖረውም ምንም ዋስትና አንዳች ደኅንንት
አይኖረውም፡፡
Tuesday, 24 February 2015
Friday, 20 February 2015
ይድረስ ለአይ ኤስ አይ ኤስና መሰል ባልንጀሮቻችሁ!
ብላቴን ጌታ ኅሩይ
ወልደ ሥላሴ በአንድ የቲያትር ድርሰታቸው ላይ እንዲህ ማለታቸው ይታወሰኛል፦ (በትክክል ካላልኩት ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡)
“አንቺ ወንጌል
አጋዳይ
እኔን ይዘሽ ወደሰማይ ወደሰማይ”
ብላቴን በቲያትር
ድርሰታቸው ውስጥ “ወንጌል የምትባል ሚስት አግብተው የደረሰባቸውንና ያገኛቸውን መከራ በቅኔ” ሲያወጉ ይታያል፡፡ ወንጌል ከሥጋ
ከደም ጋር ያይደለ፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊው ሥፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት
ጋር ነውና የምትጋደለው (ኤፌ.6፥12) የክፋት ሠራዊት አጋንንት የሁል ጊዜ ጠላቶቿ ናቸው፡፡ ወንጌል ከአጋንንት ጋር ዘወትር ተጋዳይ
ናት ማለት ነው፡፡
Saturday, 14 February 2015
ለአዋጁ ጾም አዋጅ ይታወጅ!
ከፊታችን ሳምንት ጀምሮ ላሉት ተከታታይ ሳምንታት “ሁሉም ምዕመን የሚጾመውና”
በቤተ ክርስቲያናችን ታላላቅ ከሚባሉ የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ የሆነው ጾም ፤ ጾመ ሁዳዴ ወይም ዓቢይ ጾም ወይም የጌታ ጾም
የሚባለው ነው፡፡ ጌታ ጾምን በጾመበት ወራት ዲያብሎስ በስስት ፣ በትዕቢትና ገንዘብን በመውደድ ኃጢአት በግልጥ ፈትኖታል፡፡(ማቴ.4፥1-11)
ንጹሐ ባህርይ መድኃኒት ክርስቶስ ደግሞ ዲያብሎስን ድል አድርጎታል፡፡ “ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነም ነውና
ከዚህ የተነሳ በድካማችን ሊራራልን የሚችል ሊቀ ካህናት ሆኖልናል።” (ዕብ.4፥15)
Friday, 6 February 2015
ጌታ የማያውቃቸው “የጌታ አገልጋዮች”
ምስክርነት አንዱ የአምልኮ መገለጫ
ነው፡፡ አንድ አማኝ “ክርስቶስ እርሱ ኢየሱስ ነው ወይም ክርስቶስ እርሱ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነው” (ማቴ.16፥16 ፤ ሐዋ.9፥20
፤22)ብሎ ወደቤተ ክርስቲያን አካል ሲጨመር አንዱ የየዕለት ዋና ተግባሩ ምስክርነት ነው፡፡ ያመንነውን በመናገር ብቻ የምንመሰክር
አይደለንም ፤ በሕይወትና በምግባር(በሥራ) እንጂ፡፡ “በጸጋ ድነናል”(ኤፌ.2፥5) ካልን ልክ እንደመዳናችን ማመናችንም ከእኛ የሆነ
አይደለም፡፡ ጸጋው በእምነት ካዳነን “ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ” ከእኛ ሥራ የተነሳ አይደለም፡፡(ኤፌ.2፥8)
እኛን ለማዳን አብ ልጁን ወደምድር ሲልክ ፤ እኛ ምንም የተገባን አልነበርንም፡፡
ስለዚህ “በእንዲሁ ፍቅር”(ዮሐ.3፥16) ወዶን በልጁ ሞት አዳነን፡፡ የልጁን ማዳንም እንድንቀበልም በልባችን የእምነትን አቅም
ያኖረው እርሱ ነው፡፡ ነጻ ምርጫችንን ጠብቆ ፥ አምነን ወደእርሱ በመጣን ጊዜ ግን እንድናምነው ጉልበት የሆነን ያዳነን ያው ጌታ
ነው፡፡ እንዲሁ “መልካሙን ሥራ ለማድረግም በክርስቶስ ኢየሱስ በሆነልን አዲስ ፍጥረት መወለድ(መፈጠር) ያስፈልገናል፡፡ (ኤፌ.2፥10)
Sunday, 1 February 2015
ከነቢዩ የተሻሉት አህዛብና ግዕዛን
ትንቢተ ዮናስን ስናጠና የእግዚአብሔር
አስተማሪነትና ታጋሽነትን በእውነት ልብ የሚነካ ነው፡፡ እግዚአብሔር የሚንቀው አንዳች ሥነ ፍጥረት እንደሌለ ስናይ ደግሞ የዮናስን
መጽሐፍ ይበልጥ ደጋግመን ባለመሰልቸት በትኩረት እንድናየው ያደርገናል፡፡ ምንም እንኳ አህዛብ ቢሆኑም እግዚአብሔር የታላቂቱን ከተማ
የነነዌን ክፋት ወደፊቱ መውጣቱ ባየ ጊዜ ከፍርድና ከቁጣ ይልቅ ይመለሱ እንደሁ በማለት የንስሐ ዕድል ሊሰጥ ነቢዩ ዮናስን ወደነነዌ
“ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ።” አለው፡፡(ዮና.1፥2)
እግዚአብሔር ሳያስተምር ፣ ሳይመክር ፣ ሳይዘክር ፣ ሳይገስጽ ፣ ሳያስጠነቅቅ
… ለፍርድ አይቸኩልም፡፡ እግዚአብሔር የኃጢአታችን ብዛት አያስጨንቀውም ፤ የትኛውም የኃጢአት ብዛት ትንሹን የእርሱን ምህረት እንደማይበልጥ
ያውቀዋልና፡፡ ስለዚህ ነነዌን በፍርድ ከማስተማር በፍቅር ሊያስተምር ታላቁን ነቢይ ላከላት፡፡ ሥልጣን ከኃይል እንዲበልጥ በፍቅር
ማስተማርም በፍርድና በተግሳጽ ከማስተማር እጅጉን ይበልጣል፡፡ ጌታ እግዚአብሔር ነነዌን ማስተማር የፈለገው በምህረትና በፍቅር ነው
፤ ዮናስ ግን እግዚአብሔር ከተማይቱን በፍርድና በቁጣ እንዲያስተምር እንጂ በፍቅር ከማስተማርና “ንስሐ ግቡ” ከሚለው ጀምር መባሉን
አልወደደውም፡፡ ስለዚህም ከእግዚአብሔር ፊት መሸሽን እንደመፍትሔ በመቁጠር የዚያን ጊዜ የአለም ዳርቻ ናት ተብላ ወደምትታመነው
ከነነዌ ማዶ ሊሄድ ተነሳ፡፡ ዳዊት “ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ? ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ? … ”(መዝ.138፥7) ያለውን ዘንግቶት
ነበር፡፡
Wednesday, 28 January 2015
መምህር ፣ ኢንጂነር ፣ አርቲስት ፣ ዲያቆን ...
መጽሐፍ ቅዱስንም ሆነ የቤተ ክርስቲያንን
ታሪክ ስናጠና ጸጋ ልዩ ልዩ እንደሆነ ፤ ነገር ግን መጋረጃን እንደሚያያይዘው ኩላብ የተያያዙና አንድን አካል እንደመሥራት ያሉ
እንደሆኑ እናስተውላለን፡፡ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የተለያዩ ጸጋዎችን ለቤተ ክርስቲያን አማኞች የሚሰጠው የጸጋ ድኃ እንደሌለና
የቤተ ክርስቲያንን ምልአት ለማሳየት ነው፡፡ በጸጋ ትምህርት ትንሽ የሚባል ጸጋ ከሌለ ሁሉም እኩል ሊከበሩና አገባብ ያለው ሥፍራ
፤ ክብር ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን በጳጳስነት ጸጋ እንደ ኤፌሶን ሽማግሌዎች የሚመራ አማኝ ፥(ሐዋ.20፥28) የእርሱ
ጸጋ ቃሉን እንደልድያ በመስማት ልቡ ከተከፈተለት ሰው ጋር (ሐዋ.16፥14) ምንም የጸጋ ልዩነት የለውም፡፡
Thursday, 22 January 2015
ዕድሜና ፍሬያችን
ከትላንት በስቲያ …
አሜሪካ ʻምትባል ትልቅዬ አገር
በአንድ መልሳ ፣ የሥጋ መንፈስዋን ፣ ክፍልፍሉን መንደር
ʻስቴቶቿን ሁሉ ቀምራ አዋህዳ
ተተኮሰች “አሉ” አድጋ ተመንድጋ
እኛን እዚህ ትታ እርሷ ወደህዋ …
Sunday, 18 January 2015
“የምወድህ ልጄ አንተ ነህ …” (ማር.1፥10)
ጌታ የማስተማር አገልግሎቱን ሲጀምር ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ሲሆን (ሉቃ.3፥23)
በግልጥ ለማገልገልና ለመጠመቅ ከመውጣቱ በፊት ይኖር የነበረው ደግሞ በገሊላ ናዝሬት ነው፡፡ (ማቴ.2፥23) ናዝሬት በብሉይ ኪዳን
በአንድም ሥፍራ ስሟ ያልተጠቀሰችና የማትታወቅ ከተማ ናት፡፡ ናዝሬት የማትታወቅና ያልተጠቀሰች ከተማ ብትሆንም፥ ለጌታ ኢየሱስ “ቅጥያ
ስያሜ” ሆና “የናዝሬቱ ኢየሱስ” ለመባል የበቃች ከተማ ናት፡፡ ጌታ “የናዝሬቱ ኢየሱስ” የተባለው ስለተወለደባትና ስላደገባት ብቻ እንጂ እንደነሶምሶን
“ልዩ ናዝራዊ” ለመባል አይደለም፡፡
Monday, 12 January 2015
ፊደል ከንባብ ፤ መንፈስ ከትርጓሜ ይስማማልን?
“የሥጋ ሕግ
ያጠፋል፤ የነፍስ ሕግ ግን ያድነናልና”
(በግርማዊ ቀዳ. ኃይለ ሥላሴ ንጉሰ
ነገስት ዘኢትዮጲያ
መልካም ፈቃድ
በአሜሪካ ከታተመው የ1938 ዓ.ም
መጽሐፍ ቅዱስ ከታተመ የተወሰደ፡፡
ገጽ. 386)
በማስጨነቅ ወይም እጅ በመጠምዘዝ ከሚተረጎሙ የመጽሐፍ
ቅዱስ ክፍሎች አንዱ ከላይ በርዕሳችን ያነሳነው ቃል በብዛት ይዘወተራል፡፡ ይህንን ቃል ብዙ ምዕመናን ብቻ ሳይሆኑ በሕዝብ ዘንድ
“ተቀባይነት ያላቸው” የቤተ ክርስቲያን መሪዎችና ሰባኪዎች ጭምር በመጽሐፎቻቸውና በስብከቶቻቸው መሐል ከመጽሐፉ ሐሳብ ውጪ በመውጣትና
ወደራስ ሃሳብ በመሳብ ሲተረጉሙት አይተናል፤ ሰምተናልም፡፡
Tuesday, 6 January 2015
የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ልዩ ነው!
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት
መታሠቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!!
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ተወልዷል፡፡ መወለዱም “ልደተ አዳም እምድር ፤ ልደተ ሔዋን እምገቦ ፤ ልደተ አቤል እምከርሥ ፤ ልደተ በግዕ እምዕፅ ፤ ልደተ
ሙታን እመቃብር” እንደሆነው ያይደለ የእርሱ ከዚህ የተለየ ልዩ ልደት ነው፡፡ (ወንጌል አንድምታ፤ ከቀድሞ አባቶች ጀምሮ ሲወርድ
ሲዋረድ የመጣው ንባብና ትርጓሜው ፤ 1997፤ በትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ድርጅት የታተመ፤ ገጽ.44) እርሱ የተወለደው ከእመቤታችን
ከቅድስት ድንግል ማርያም ፤ ከሰው ነው፡፡ ለዚህም ነው ወንጌላዊው “ቃል ሥጋ ሆነ” ብሎ ሳያበቃ ፤ “ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ
በእኛ አደረ” ሲል የእኛን ሥጋ መዋሐዱን በማስረገጥ የተናገረው፡፡(ዮሐ.1፥1 ፤ 14)
Friday, 2 January 2015
Monday, 29 December 2014
እኛ ኢትዮጲያውያን በአጼ ቴዎድሮስ እይታ …
“እኛ ኢትዮጲያውያን” የሚለው ሃሳብ “ደምና አጥንታችንን ገብረንላታል”
ለሚሉ አርበኞች ልብ የሚመላ ነገር አለው፤ በጥንት በሕገ ልቡና፣ ቀጥሎም በሕገ ኦሪት ከዚያም በክርስትና መኖሯን ለሚያምኑ ደፍረው
የሚሉት ነገር አላቸው ፤ በአክሱምና በዛጉዌ የታነጹትን ሐውልትና ህንጻ አብያተ ክርስቲያናትን ለሚያደንቁ አርክቴክቸሮችና ሌሎች፥
እጃቸውን በአፋቸው ጭነው ብዙ የሚተነትኑት ነገር አላቸው፤ ሁሉም በየሙያውና በያለበት ደረጃ ስለኢትዮጲያችን ቢጠየቅ የሚለው ብዙ
ብዙ አለው፡፡
ሃሳቤ ግን ወዲህ ነው፤ አጼ ቴዎድሮስ በጥር 22 በ1858 ዓ.ም ለእንግሊዛዊቷ
ንግሥት ለቪክቶሪያ በኢትዮጲያ ምድር ከታሠሩት የእንግሊዝ እስረኞች ጋር በተያያዘ፤ እንዲሁም ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ሲያስቀምጡ፦ “የኢትዮጲያን ሰዎች ድንቁርነታችነን ዕውርነታችነን ሣይሰሙት አይቀሩም ያማረ
መስሎኝ ደፍሬ የላክሁብዎን ከፍቶብኝ (አጥፍቼ እንደሆነ) ቢገኝ ይምከሩኝ እንጂ አይክፉብኝ፡፡ እግዚአብሔር የመረጠዎ ንግሥት ዓይንዎ
የበራ ነውና፡፡”(ጳውሎስ ኞኞ ፤ ዐጤ ቴዎድሮስ
፤ ግንቦት 1985 ፤ ቦሌ ማተሚያ ድርጅት ፤ አዲስ አበባ ፤ ገጽ.214)
አሁንም በድጋሚ በሚያዝያ 10 ቀን 1858 ዓ.ም ለዚህችው ንግሥት ድጋሚ
በጻፉት ድብዳቤ እኛን ኢትዮጲያውያንን እንዲህ ገልጠዋል፦ “ የኢትዮጲያ ሰዎች እውር ነንና ዓይናችነን ያብሩልነ፡፡ እግዚአብሔር
በሰማይ ያብራልዎ፡፡” በማለትም በግልጥ አስቀምጠዋል፡፡ (ጳውሎስ ኞኞ ፤ ዐጤ ቴዎድሮስ ፤ ግንቦት 1985 ፤ ቦሌ ማተሚያ ድርጅት ፤ አዲስ አበባ፤ ገጽ 233)
Subscribe to:
Posts (Atom)





