Saturday, 14 February 2015

ለአዋጁ ጾም አዋጅ ይታወጅ!

                               
                       Please read in PDF

    ከፊታችን ሳምንት ጀምሮ ላሉት ተከታታይ ሳምንታት “ሁሉም ምዕመን የሚጾመውና” በቤተ ክርስቲያናችን ታላላቅ ከሚባሉ የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ የሆነው ጾም ፤ ጾመ ሁዳዴ ወይም ዓቢይ ጾም ወይም የጌታ ጾም የሚባለው ነው፡፡ ጌታ ጾምን በጾመበት ወራት ዲያብሎስ በስስት ፣ በትዕቢትና ገንዘብን በመውደድ ኃጢአት በግልጥ ፈትኖታል፡፡(ማቴ.4፥1-11) ንጹሐ ባህርይ መድኃኒት ክርስቶስ ደግሞ ዲያብሎስን ድል አድርጎታል፡፡ “ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነም ነውና ከዚህ የተነሳ በድካማችን ሊራራልን የሚችል ሊቀ ካህናት ሆኖልናል።” (ዕብ.4፥15)

Friday, 6 February 2015

ጌታ የማያውቃቸው “የጌታ አገልጋዮች”


                                 Please Read in PDF

     ምስክርነት አንዱ የአምልኮ መገለጫ ነው፡፡ አንድ አማኝ “ክርስቶስ እርሱ ኢየሱስ ነው ወይም ክርስቶስ እርሱ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነው” (ማቴ.16፥16 ፤ ሐዋ.9፥20 ፤22)ብሎ ወደቤተ ክርስቲያን አካል ሲጨመር አንዱ የየዕለት ዋና ተግባሩ ምስክርነት ነው፡፡ ያመንነውን በመናገር ብቻ የምንመሰክር አይደለንም ፤ በሕይወትና በምግባር(በሥራ) እንጂ፡፡ “በጸጋ ድነናል”(ኤፌ.2፥5) ካልን ልክ እንደመዳናችን ማመናችንም ከእኛ የሆነ አይደለም፡፡ ጸጋው በእምነት ካዳነን “ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ” ከእኛ ሥራ የተነሳ አይደለም፡፡(ኤፌ.2፥8)
  እኛን ለማዳን አብ ልጁን ወደምድር ሲልክ ፤ እኛ ምንም የተገባን አልነበርንም፡፡ ስለዚህ “በእንዲሁ ፍቅር”(ዮሐ.3፥16) ወዶን በልጁ ሞት አዳነን፡፡ የልጁን ማዳንም እንድንቀበልም በልባችን የእምነትን አቅም ያኖረው እርሱ ነው፡፡ ነጻ ምርጫችንን ጠብቆ ፥ አምነን ወደእርሱ በመጣን ጊዜ ግን እንድናምነው ጉልበት የሆነን ያዳነን ያው ጌታ ነው፡፡ እንዲሁ “መልካሙን ሥራ ለማድረግም በክርስቶስ ኢየሱስ በሆነልን አዲስ ፍጥረት መወለድ(መፈጠር) ያስፈልገናል፡፡ (ኤፌ.2፥10)

Sunday, 1 February 2015

ከነቢዩ የተሻሉት አህዛብና ግዕዛን


                                 PLease read in PDF

     ትንቢተ ዮናስን ስናጠና የእግዚአብሔር አስተማሪነትና ታጋሽነትን በእውነት ልብ የሚነካ ነው፡፡ እግዚአብሔር የሚንቀው አንዳች ሥነ ፍጥረት እንደሌለ ስናይ ደግሞ የዮናስን መጽሐፍ ይበልጥ ደጋግመን ባለመሰልቸት በትኩረት እንድናየው ያደርገናል፡፡ ምንም እንኳ አህዛብ ቢሆኑም እግዚአብሔር የታላቂቱን ከተማ የነነዌን ክፋት ወደፊቱ መውጣቱ ባየ ጊዜ ከፍርድና ከቁጣ ይልቅ ይመለሱ እንደሁ በማለት የንስሐ ዕድል ሊሰጥ ነቢዩ ዮናስን ወደነነዌ “ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ።” አለው፡፡(ዮና.1፥2)
   እግዚአብሔር ሳያስተምር ፣ ሳይመክር ፣ ሳይዘክር ፣ ሳይገስጽ ፣ ሳያስጠነቅቅ … ለፍርድ አይቸኩልም፡፡ እግዚአብሔር የኃጢአታችን ብዛት አያስጨንቀውም ፤ የትኛውም የኃጢአት ብዛት ትንሹን የእርሱን ምህረት እንደማይበልጥ ያውቀዋልና፡፡ ስለዚህ ነነዌን በፍርድ ከማስተማር በፍቅር ሊያስተምር ታላቁን ነቢይ ላከላት፡፡ ሥልጣን ከኃይል እንዲበልጥ በፍቅር ማስተማርም በፍርድና በተግሳጽ ከማስተማር እጅጉን ይበልጣል፡፡ ጌታ እግዚአብሔር ነነዌን ማስተማር የፈለገው በምህረትና በፍቅር ነው ፤ ዮናስ ግን እግዚአብሔር ከተማይቱን በፍርድና በቁጣ እንዲያስተምር እንጂ በፍቅር ከማስተማርና “ንስሐ ግቡ” ከሚለው ጀምር መባሉን አልወደደውም፡፡ ስለዚህም ከእግዚአብሔር ፊት መሸሽን እንደመፍትሔ በመቁጠር የዚያን ጊዜ የአለም ዳርቻ ናት ተብላ ወደምትታመነው ከነነዌ ማዶ ሊሄድ ተነሳ፡፡ ዳዊት “ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ? ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ? … ”(መዝ.138፥7) ያለውን ዘንግቶት ነበር፡፡

Wednesday, 28 January 2015

መምህር ፣ ኢንጂነር ፣ አርቲስት ፣ ዲያቆን ...


                                         Please read in PDF
   
    መጽሐፍ ቅዱስንም ሆነ የቤተ ክርስቲያንን ታሪክ ስናጠና ጸጋ ልዩ ልዩ እንደሆነ ፤ ነገር ግን መጋረጃን እንደሚያያይዘው ኩላብ የተያያዙና አንድን አካል እንደመሥራት ያሉ እንደሆኑ እናስተውላለን፡፡ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የተለያዩ ጸጋዎችን ለቤተ ክርስቲያን አማኞች የሚሰጠው የጸጋ ድኃ እንደሌለና የቤተ ክርስቲያንን ምልአት ለማሳየት ነው፡፡ በጸጋ ትምህርት ትንሽ የሚባል ጸጋ ከሌለ ሁሉም እኩል ሊከበሩና አገባብ ያለው ሥፍራ ፤ ክብር ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን በጳጳስነት ጸጋ እንደ ኤፌሶን ሽማግሌዎች የሚመራ አማኝ ፥(ሐዋ.20፥28) የእርሱ ጸጋ ቃሉን እንደልድያ በመስማት ልቡ ከተከፈተለት ሰው ጋር (ሐዋ.16፥14)  ምንም የጸጋ ልዩነት የለውም፡፡

Thursday, 22 January 2015

ዕድሜና ፍሬያችን


                                      Please read in PDF

ከትላንት በስቲያ …
አሜሪካ ʻምትባል ትልቅዬ አገር
በአንድ መልሳ ፣ የሥጋ መንፈስዋን ፣ ክፍልፍሉን መንደር
ʻስቴቶቿን ሁሉ ቀምራ አዋህዳ
ተተኮሰች “አሉ” አድጋ ተመንድጋ
እኛን እዚህ ትታ እርሷ ወደህዋ …

Sunday, 18 January 2015

“የምወድህ ልጄ አንተ ነህ …” (ማር.1፥10)





እንኳን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት መታሠቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡



    ጌታ የማስተማር አገልግሎቱን ሲጀምር ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ሲሆን (ሉቃ.3፥23) በግልጥ ለማገልገልና ለመጠመቅ ከመውጣቱ በፊት ይኖር የነበረው ደግሞ በገሊላ ናዝሬት ነው፡፡ (ማቴ.2፥23) ናዝሬት በብሉይ ኪዳን በአንድም ሥፍራ ስሟ ያልተጠቀሰችና የማትታወቅ ከተማ ናት፡፡ ናዝሬት የማትታወቅና ያልተጠቀሰች ከተማ ብትሆንም፥ ለጌታ ኢየሱስ “ቅጥያ ስያሜ” ሆና “የናዝሬቱ ኢየሱስ” ለመባል የበቃች ከተማ ናት፡፡ ጌታ “የናዝሬቱ  ኢየሱስ” የተባለው ስለተወለደባትና ስላደገባት ብቻ እንጂ እንደነሶምሶን “ልዩ ናዝራዊ” ለመባል አይደለም፡፡

Monday, 12 January 2015

ፊደል ከንባብ ፤ መንፈስ ከትርጓሜ ይስማማልን?

                         
                                Please read in PDF

                             “የሥጋ ሕግ ያጠፋል፤ የነፍስ ሕግ ግን ያድነናልና”
                           (በግርማዊ ቀዳ. ኃይለ ሥላሴ ንጉሰ ነገስት ዘኢትዮጲያ
                            መልካም ፈቃድ በአሜሪካ ከታተመው የ1938 ዓ.ም
                            መጽሐፍ ቅዱስ ከታተመ የተወሰደ፡፡ ገጽ. 386)
    በማስጨነቅ ወይም እጅ በመጠምዘዝ ከሚተረጎሙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አንዱ ከላይ በርዕሳችን ያነሳነው ቃል በብዛት ይዘወተራል፡፡ ይህንን ቃል ብዙ ምዕመናን ብቻ ሳይሆኑ በሕዝብ ዘንድ “ተቀባይነት ያላቸው” የቤተ ክርስቲያን መሪዎችና ሰባኪዎች ጭምር በመጽሐፎቻቸውና በስብከቶቻቸው መሐል ከመጽሐፉ ሐሳብ ውጪ በመውጣትና ወደራስ ሃሳብ በመሳብ ሲተረጉሙት አይተናል፤ ሰምተናልም፡፡

Tuesday, 6 January 2015

የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ልዩ ነው!

       
                                  Please read in PDF



             እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት 
               መታሠቢያ በዓል በሰላም  አደረሳችሁ!!!!

        ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተወልዷል፡፡ መወለዱም “ልደተ አዳም እምድር ፤ ልደተ ሔዋን እምገቦ ፤ ልደተ አቤል እምከርሥ ፤ ልደተ በግዕ እምዕፅ ፤ ልደተ ሙታን እመቃብር” እንደሆነው ያይደለ የእርሱ ከዚህ የተለየ ልዩ ልደት ነው፡፡ (ወንጌል አንድምታ፤ ከቀድሞ አባቶች ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው ንባብና ትርጓሜው ፤ 1997፤ በትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ድርጅት የታተመ፤ ገጽ.44) እርሱ የተወለደው ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ፤ ከሰው ነው፡፡ ለዚህም ነው ወንጌላዊው “ቃል ሥጋ ሆነ” ብሎ ሳያበቃ ፤ “ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ” ሲል የእኛን ሥጋ መዋሐዱን በማስረገጥ የተናገረው፡፡(ዮሐ.1፥1 ፤ 14)

Friday, 2 January 2015

ኢየሱስ የማታሳስት በር


                  Please read in PDF

መግቢያዬ፣
መውጪያዬ፣
ሆነህ ስላየሁህ በህይወት ዘመኔ፤ 

Monday, 29 December 2014

እኛ ኢትዮጲያውያን በአጼ ቴዎድሮስ እይታ …

      
                                  
                             Please read in PDF                       

       “እኛ ኢትዮጲያውያን” የሚለው ሃሳብ “ደምና አጥንታችንን ገብረንላታል” ለሚሉ አርበኞች ልብ የሚመላ ነገር አለው፤ በጥንት በሕገ ልቡና፣ ቀጥሎም በሕገ ኦሪት ከዚያም በክርስትና መኖሯን ለሚያምኑ ደፍረው የሚሉት ነገር አላቸው ፤ በአክሱምና በዛጉዌ የታነጹትን ሐውልትና ህንጻ አብያተ ክርስቲያናትን ለሚያደንቁ አርክቴክቸሮችና ሌሎች፥ እጃቸውን በአፋቸው ጭነው ብዙ የሚተነትኑት ነገር አላቸው፤ ሁሉም በየሙያውና በያለበት ደረጃ ስለኢትዮጲያችን ቢጠየቅ የሚለው ብዙ ብዙ አለው፡፡
     ሃሳቤ ግን ወዲህ ነው፤ አጼ ቴዎድሮስ በጥር 22 በ1858 ዓ.ም ለእንግሊዛዊቷ ንግሥት ለቪክቶሪያ በኢትዮጲያ ምድር ከታሠሩት የእንግሊዝ እስረኞች ጋር በተያያዘ፤ እንዲሁም ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ሲያስቀምጡ፦  “የኢትዮጲያን ሰዎች ድንቁርነታችነን ዕውርነታችነን ሣይሰሙት አይቀሩም ያማረ መስሎኝ ደፍሬ የላክሁብዎን ከፍቶብኝ (አጥፍቼ እንደሆነ) ቢገኝ ይምከሩኝ እንጂ አይክፉብኝ፡፡ እግዚአብሔር የመረጠዎ ንግሥት ዓይንዎ የበራ ነውና፡፡”(ጳውሎስ ኞኞ ፤ ዐጤ ቴዎድሮስ ፤ ግንቦት 1985 ፤ ቦሌ ማተሚያ ድርጅት ፤ አዲስ አበባ ፤ ገጽ.214)
    አሁንም በድጋሚ በሚያዝያ 10 ቀን 1858 ዓ.ም ለዚህችው ንግሥት ድጋሚ በጻፉት ድብዳቤ እኛን ኢትዮጲያውያንን እንዲህ ገልጠዋል፦ “ የኢትዮጲያ ሰዎች እውር ነንና ዓይናችነን ያብሩልነ፡፡ እግዚአብሔር በሰማይ ያብራልዎ፡፡” በማለትም በግልጥ አስቀምጠዋል፡፡ (ጳውሎስ ኞኞ ፤ ዐጤ ቴዎድሮስ ፤ ግንቦት 1985 ፤ ቦሌ ማተሚያ ድርጅት ፤ አዲስ አበባ፤ ገጽ 233)

Tuesday, 23 December 2014

የትኩረት ጩኸት ትኩረትን ሲያደበዝዝ


                                  Please read in PDF              

     በአገራችን ትኩረትን የሚስበው ድርጊት እንጂ ዝግጅት አይደለም፤ አንድ ከባድና ዘግናኝ ድርጊት ሲፈጸም ብዙ ጊዜ ስሜቶቻችን ተጋግሎ መንጫጫት፤ ድርጊቱ እንዳይፈጸም ቀድመን ከመሥራት ይልቅ ከድርጊቱ በኋላ በጣም መጯጯህ ፣ ሰላማዊ ሰልፎች ፣ ብዙ ስብሰባዎች ፣ የአቋም መግለጫዎችና የስሜት ዕርምጃዎችም ይወሰዳሉ፡፡  ማሳያዎችን በምሳሌ ብናነሳ፦ በባለፈው ወር የአዋሽ ፓርክን በሚያቋርጠው ትልቁ የምሥራቅ ኢትዮጲያ መንገድ በጉዞ ላይ ሳለ በአንድ ቅጥቅጥ አይሱዙ ላይ በደረሰው አደጋ ከሐያ ሰባት ሰዎች በላይ የሞት አደጋ መድረሱን ሰምተን ሳናባራ፤ ወዲያውኑ በተወሰደው እርምጃ መንገዶች ላይ በተደረገው (በዋናው አስፓልት ላይ መኪናዎች በጉዟቸው እንዲያቀዘቅዙ ለማድረግ በተደረገው ሌላ የአስፓልት ጉማጅ ሥራ) በተወሰደው የስሜት ዕርምጃ ሌሎች የመኪና አደጋዎች መከሰታቸውን ከቦታው ሄዶ ማስተዋል ይቻላል፡፡
    አሁንም ሌላ ማሳያ ብናነሳ ፦ በባለፈው ወር ከተከሰተው ጆሮን ጭው ከሚያደርጉ ነገሮች አንዱ የእህት ሐና ላላንጎ ጉዳይ  ነው፡፡ ድርጊቱ ከዳር እስከዳር ብዙ በጣም ብዙ አነጋግሯል፡፡ ከወረዳ እስከ ሚኒስቴር ቢሮ ፤ ከሆስፒታል እስከ የፖሊስ መምሪያና ጣቢያዎች ፤ ከመንገድ ዳር “ታዛቢ” እስከመኪና አሽከርካሪዎች በዚህ ሂደት ውስጥ ያሉበትን ልልነትና ግድ የለሽነት በሚገባ አጢነናል፡፡ ጥቂት ስህተት ምን ያህል ዋጋ እንደሚያስከፍል አይተናል፡፡ የፖሊስ ዳተኝት ፣ የሆስፒታሎቻችን ከልክ ያለፈ ቸለተኝነት ድርጊቱን ከፈጸሙት የማይተናነስ መሆኑን ሌላ ምስክር ሳያሻ የአደባባይ ገመና ሆኗል፡፡

Thursday, 18 December 2014

በመሠወሬ ነው!


                     Please read in PDF

ሺህ ሰልፍ ከፊቴ ፥ ትዕልፊት ከኋላ፤
እንደጉንዳን ፈልቶ ፥ እንዳʻንበሳ ቢያጓራ፤

Monday, 15 December 2014

የብርሃን መልአክ የሚመስሉ አገልጋዮች(የመጨረሻ ክፍል)



4. አገልግሎቱን ለእግዚአብሔር ለቃሉ አደራ መስጠትን ያውቃል (ቁ.32)

                  “ብዙ ሰዎች የመሰከሩለትን ከእኔም የሰማኸውን ሌሎችን ደግሞ
                  ሊያስተምሩ ለሚችሉ ለታመኑ ሰዎች አደራ ስጥ።” (2ጢሞ.2፥1)

   አገልጋዮች የእግዚአብሔርን መንጋ የምንጠብቅ ሲመስለን እንስታለን፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ የኤፌሶንን ሽማግሌዎች (ጳጳሳት) “እናንተን ራሳችሁን … ለጸጋው ቃል አደራ ሰጥቻችኋችሁ” ሲላቸው እናያለን፡፡ የእግዚአብሔር መንጋ የሚጠፋው ወይም የሚጎዳው ከእግዚአብሔር በኃጢአቱ ሲለይ ወይም እግዚአብሔር ንስሐ ባለመግባቱ በኃጢአቱ ምክንያት ሲለየው  ነው፡፡ ያ እንዳይሆን መሪዎቹ ሕዝቡን ትክክለኛው የጸጋውን ቃል ወንጌል በማስተማር ሊመሩት ይገባል፡፡ በትክክል ሳይነግሩትና ሳያስተምሩት ሲቀር ግን ይጎዱታል ማለትም የመንግሥተ ሰማያት በር ይዘጉበታል፡፡
      ቅዱስ ጳውሎስ እርሱ ቀድሞ ወንጌልን ለመስበክ አደራ ከክርስቶስ ኢየሱስ እንደተቀበለ እንዲሁ፤ (ሐዋ.9፥1-16 ፤ 26፥16 ፤ 1ቆሮ.9፥17) አሁን ደግሞ እርሱ ለታመኑት ሲሰጥና የታመኑትም ለሌሎች ለታመኑ አደራ እንዲሠጡ ሲተጋ እናየዋለን፡፡ ወንጌል መስበክ አደራ ከሆነ አደራው ኃላፊነት ያለበት አደራ ነው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ወንጌልን ኃላፊነት ተሰምቷቸው ከፍቅር በተነሳ ውዴታ እንጂ በምርጫ እንዲያገለግሉ አልተጠሩም፡፡

Tuesday, 9 December 2014

የብርሃን መልአክ የሚመስሉ አገልጋዮች(ክፍል - አራት)




2. ለመንጋው ሁሉና ለራሱ ሊጠነቀቅ ይገባል፡፡(ቁ.28)

    ቅዱስ ጳውሎስ ቅዱስ ጢሞቴዎስን “ለራስህና ለትምህርትህ ተጠንቀቅ፥ በእነዚህም ጽና፤ ይህን ብታደርግ፥ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህና።” በማለት ይመክረዋል፡፡ በእርግጥ የሚያድን እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ አማኞች ወደጌታ በመምጣት ሕይወታቸው  ዕለት ዕለት በማደግ እግዚአብሔርን ወደመምሰል እንዲደርሱ አገልጋዮች ትልቁን ድርሻ አላቸውና፥ ለራሳቸውም፤ ለትምህርታቸውም ሊጠነቀቁ ይገባቸዋል፡፡ ጤናማውን ጉዞ እስከፍጻሜው ልንጓዝ የምንችለው ለትምህርታችንና ለምናስተምረው የእግዚአብሔር መንጋ መጠንቀቅ ስንችል ነው፡፡
    ጥቂት እርሾ ብዙውን ሊጥ እንደሚያቦካ (1ቆሮ.5፥16)፤ ጥቂት የተባለም ኃጢአት ወይም ክፉ ትምህርት ብዙውን መንጋ ከመበከል አይመለስም፡፡ እንደዋዛ የሚደረጉና የሚነገሩ ነገሮች በመንጋው ላይ ሊያሳርፉ የሚችሉት ተጽዕኖ ቀላል አይደለም፡፡ ትላንት እንደዋዛ ሲነገሩ የነበሩ ተረታ ተረቶች፥ ዛሬ ወደቤተ ክርስቲያን ሾልከው ገብተው ለብዙ ምዕመናን የሕይወት መመሪያ እስከመሆን ደርሰዋል፡፡ በዚህ ሳያበቃ አሁንም ለመንጋው ባለመራራት የሚጻፉትና የሚሰበኩት ስብከቶች በቃሉ ሚዛንነት ልንፈትሻቸው፤ ቀለው ከተገኙ ልናስወግዳቸው ይገባናል፡፡

Tuesday, 2 December 2014

የብርሃን መልአክ የሚመስሉ አገልጋዮች(ክፍል - ሦስት)



5. የሚነሱት ከመካከላችን ነው፡፡
     እውነተኛውና ለእግዚአብሔር የጨከነ አገልጋይ ሲጠፋ ክፉው አገልጋይ ከውጪ ወደውስጥ ወይም በብዛት ከመንጋው መካከል ይነሳል፡፡ ከመካከል የሚነሱ የሐሰት መምህራን በዋናነት የመሳታቸውና የማሳታቸው ምክንያት ከመሠረተ እምነት ትምህርት ጉድለት ነው፡፡ ገበሬ እርሻውን አለስልሶ ከዘራ በኋላ በየጊዜው መከታተል ይገባዋል፡፡ የሚከታተለው አለስልሶ የዘራው እርሻ የማይበቃ ሆኖ ሳይሆን አረምና እንክርዳድ ዋናውን ዘር እንዳይውጠው ነው፡፡ አረምና እንክርዳድ ገበሬው የዘራው አይደልም፤ እርሱ ያልዘራው ከመካከል የበቀለው አረም ግን የዘራውና ዋና ዘር ሊያጠፋው ይችላል፡፡ ስለዚህ በየጊዜው  ሊያርም ፤ ሊኰተኩተው ይገባዋል፡፡ በመንፈሳዊ አለም ደግሞ መልካሙ ገበሬ እግዚአብሔር ዘርን ከዘራ በኋላ መጥቶ ክፉን ዘር የሚዘራው ጠላት ዲያብሎስ ነው፡፡ (ማቴ.13፥28) ስለዚህ ልንተጋ ቃሉን በማጥናት ልንበረታ ይገባናል፡፡