v ሙሴ
ከእግዚአብሔር “እርሱን ስሙት” የተባለለት ሰው ነበር፡፡ ምክንያቱም “ይሰጠን ዘንድ ህይወት ያላቸውን ቃላት የተቀበለ”
ነውና፡፡(ሐዋ.7፥37-38) ነገር ግን “አባቶች” የነበሩቱ ሊታዘዙት አልወደዱም፤ ይልቁንም ገፉት እንጂ፡፡ ፈሪሳውያንና
ሰዱቃውያንም ፤ታናናሽና ታላላቅ አይሁድም ነቢያት የመሰከሩለትና አብ በድንቅ በተገለጠው የደብረ ታቦር መገለጡ “በእርሱ ደስ
የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት…”(ማቴ.17፥5) ብሎ የተናገረና በሥጋ የወለደችው እናቱ ድንግል ማርያምም
“የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ” በማለት የተናገረችለት ናት፡፡ነገር ግን ሙሴን ባለመታዘዝ እንደገፉት ሁሉ፤ ልጆች የተባሉቱም
ክርስቶስ ኢየሱስን ብዙ ጊዜ ጠሉት፤ገፉት፤ሊገድሉትም ይፈልጉት ነበር፡፡(ዮሐ.5፥16)
የእስራኤል ልጆች በዚያን ጊዜ በምድር ካሉት ሁሉ እጅግ ትሁት
የነበረውን(ዘኁ.12፥3) ሙሴን ባለመስማታቸው ካገኛቸውና ሙሴንም
ካስቆጣው አንዱ ኃጢአት ክፉ ምኞት ነው፡፡(ዘኁ.11፥4፤10)፡፡ ክፉ ምኞታቸው ለገዛ መቃብራቸውና ለሞት አሳልፎ
ሰጣቸው፡፡(ዘኁ.11፥34)፡፡ ጲላጦስ፦ አይሁድና “…የካህናት አለቆች በቅንዓት አሳልፈው እንደሰጡት ያውቅ
ነበር”(ማር.15፥6) ማወቅ ብቻ አይደለም ፤ “ኢየሱስን ግን ለፈቃዳቸው አሳልፎ የሰጠው”(ሉቃ.23፥25) መሪው ጲላጦስ
ከአይሁድ ጋር የተባበረበት አንዱ መንገድ ክፉ መሻታቸውንና ሃሳባቸውን እያወቀ፤ ህግ ተላልፎ ለክፉ ምኞታቸው አሳልፎ መስጠቱ
ነው፡፡ ይህ ድርጊት አይሁድን “ደሙ በእኛና በልጆቻችን ላይ ይሁን” እስኪሉ ዕውር አድርጓቸዋል፡፡(ማቴ.27፥25)



