Please read in PDF
አንድ የምወደው ባልንጀራ ወዳጅ ዳኛ አለኝ፡፡ለብርቱ ጉዳይ እንደሚፈልገኝ በስልክ አቻኩሎ ጠራኝ፡፡አላመነታሁም … ከተሰየመው ችሎት ገብቼ አንድ ጉዳይ እንድሰማ ጋበዘኝ፡፡የአርባ ሁለት አመት ጎልማሳ የስድስት አመት ወንድ ህጻን በፈጸመበት ግብረ ሰዶማዊነት መቀመጥ እንደማይችል ብሎም በፊንጢጣ መቀደድ እንደሚሰቃይ ከውሳኔው ስሰማ ረዥም ዝምታ ከችሎቱ በኋላ ወደ ውስጤ ተሰማኝ፡፡(አቤቱ ይህን ሁሉ ለምን ታሳየኛለህ? ... ጥፋትና ርኩሰት መዋረድስ በመካከላችን ስለምን ሆነ? … አቤቱ ምድሪቱ ለክፉዎች ተሰጥታለችና ጨርሶ ሳይጨልም ድረስልን!!!...የሚያቃጥል እንባ … መንፈስን የሚለበልብ የቁጣ ነበልባል … )
አንድ የምወደው ባልንጀራ ወዳጅ ዳኛ አለኝ፡፡ለብርቱ ጉዳይ እንደሚፈልገኝ በስልክ አቻኩሎ ጠራኝ፡፡አላመነታሁም … ከተሰየመው ችሎት ገብቼ አንድ ጉዳይ እንድሰማ ጋበዘኝ፡፡የአርባ ሁለት አመት ጎልማሳ የስድስት አመት ወንድ ህጻን በፈጸመበት ግብረ ሰዶማዊነት መቀመጥ እንደማይችል ብሎም በፊንጢጣ መቀደድ እንደሚሰቃይ ከውሳኔው ስሰማ ረዥም ዝምታ ከችሎቱ በኋላ ወደ ውስጤ ተሰማኝ፡፡(አቤቱ ይህን ሁሉ ለምን ታሳየኛለህ? ... ጥፋትና ርኩሰት መዋረድስ በመካከላችን ስለምን ሆነ? … አቤቱ ምድሪቱ ለክፉዎች ተሰጥታለችና ጨርሶ ሳይጨልም ድረስልን!!!...የሚያቃጥል እንባ … መንፈስን የሚለበልብ የቁጣ ነበልባል … )
መንግስት
“ከብዙ ነገር አንጻር” ግብረ ሰዶማዊነትን በግልጥ ባይቃወምም በዝምታ ሊደግፍ እንደሚችል ታዝበናል፡፡ ቢያንስ እንደአሸን እየፈሉ
የመጡትን እኒህን የሰዶም ሰዎች ሊያስተምር በሚችል መልኩ እንደወንጀል ህጉ ቀጥቶ አለማሳየትና አቀንቃኞቹን አለመግራት በግልጥ ከመደገፍ
አይተናነስም፡፡ ከሁሉ በላይ ግን ቤተ ክርስቲያን ለዚህ ነገር ትኩረት ሰጥታ አለመስራቷ ይበልጥ እጅግ የሚያደማ ነገር ነው፡፡ በተለይ
በገዳም ባሉ ጥቂት በማይባሉ መነኮሳትና መነኮሳይያት ዘንድ ከሚሰሙ ነውሮች መካከል አንዱ ግብረ ሰዶማዊነት ነው፡፡ምናልባት እንዲህ
ደፍሬ የምናገረው የቤተ ክርስቲያንን ነውር መግለጥ የሚያስደስት ሆኖ አይደለም፡፡ነገር ግን ማንቀላፋታችን አለልክ ስለበዛ ፣ይህ
ነውር ሩቅ እንጂ እዚህ አፍንጫችን ሥር ያለ ስላልመሰለንና ጣታችንን በሌሎች እየቀሰርን የንስሐ ዘመናችንን በክስና በሽንገላ እየጨረስነው
እንደሆነ ስለታየኝ ነው፡፡የማንክደው እውነት ግብረ ሰዶማዊነት በመካከላችን አለ፡፡መኖር ብቻ ሳይሆን ቁጥሩ ቢያንስም እንደሐገሪቱ
ህግ የተቀጡና በማረሚያ ቤቶች ያሉ ሰዎችም አሉ፡፡