7- ደሙ መካከለኛችን ነው፡፡
ከጥንት “… በሀሳባችን ጠላቶች” … “ … ከፍጥረታችንም የቁጣ ልጆች የነበርነውን” … “አሁን በሥጋው ሰውነት በሞቱ በኩል አስታረቀን፡፡”(ቆላ.1÷22፤ኤፌ.2÷3) ከመጀመርያው የሀሳብ ጠላትና የቁጣ ልጆች የነበርነውን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአባቱ ጋር ሊያቀራርበን እንደያዕቆብ መሰላል መካከለኛ ሆኖ ተገለጠ፡፡ቅዱስ ሄኔሬዎስ እንዲህ አለ፦
“አባታችን
ያዕቆብ ወደሜሶፖታምያ በሚጓዝ ጊዜ ፣በህልሙ እርሱን /ወልድን/ አየው፡፡
መሰላል ቆሞ(ዘፍ.28÷10-15)፤እርሱም ከምድር እስከሰማይ የተዘረጋ ዛፍ ነው፡፡በእርሱም
ምዕመናን
ሁሉ
ወደመንግስተ ሰማያት ይደርሳሉ፡፡የእርሱ መከራ መስቀል ለእኛ ወደላይ
መውጫ መንገዳችን
ሆኗልና፡፡”(ዳንኤል ክብረት(ዲያቆን)፡፡አበው ምን ይላሉ?፡፡
(1999)አሳታሚና አከፋፋይ ማህበረ ቅዱሳን፣ቦታ አልተጠቀሰም፡፡)
በእርግጥም
ወንጌል የመሰከረለት በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የተዘረጋው መሰላል ክርስቶስ ነው፡፡(ዮሐ.1÷52)ክርስቶስ መካከለኛ የሆነው ሰው ሆኖ ፤ደሙን አፍስሶ በሠራልን የቤዛነቱ ሥራ ነው፡፡ክርስቶስ በፍጹም ሰውነቱ እኛን ፤በፍጹም አምላክነቱ ደግሞ እግዚአብሔርን ወክሎ ሁለታችንን ያቀራረበ መካከለኛ አማኑኤል ነው፡፡እርሱ “ወደአባቱ ለመድረስ ጐዳና ፤ወደወለደው ለመግባት የሚሆን በር” ነው፡፡ጎዳናው ልክ እንደመሰላሉ ከምድር እስከሰማይ የሚደርስና የቀናም ነው፡፡በዚህ መካከለኛነቱም “የአብ ሊቀ ካህናት የሚሆን እርሱ የሰውን ባህርይ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀ፡፡”(መጽሐፈ ቅዳሴ ጕልህ፡፡(1994)፡፡አዲስ አበባ፣ትንሳኤ ማተሚያ ድርጅት፡፡ገጽ 146፤የቅዳሴ ሥርዐት ገጽ.82)
