Tuesday, 28 January 2014

የኢየሱስ ደም - የመጨረሻ ክፍል


7- ደሙ መካከለኛችን ነው፡፡


ከጥንት “… በሀሳባችን ጠላቶች” … “ … ከፍጥረታችንም የቁጣ ልጆች የነበርነውን” … “አሁን በሥጋው ሰውነት በሞቱ በኩል አስታረቀን፡፡”(ቆላ.1÷22፤ኤፌ.2÷3) ከመጀመርያው የሀሳብ ጠላትና የቁጣ ልጆች የነበርነውን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአባቱ ጋር ሊያቀራርበን እንደያዕቆብ መሰላል መካከለኛ ሆኖ ተገለጠ፡፡ቅዱስ ሄኔሬዎስ እንዲህ አለ፦
          “አባታችን ያዕቆብ ወደሜሶፖታምያ በሚጓዝ ጊዜ ፣በህልሙ እርሱን /ወልድን/ አየው፡፡
           መሰላል ቆሞ(ዘፍ.28÷10-15)፤እርሱም ከምድር እስከሰማይ የተዘረጋ ዛፍ ነው፡፡በእርሱም
          ምዕመናን ሁሉ ወደመንግስተ ሰማያት ይደርሳሉ፡፡የእርሱ መከራ መስቀል ለእኛ ወደላይ 
          መውጫ መንገዳችን ሆኗልና፡፡”(ዳንኤል ክብረት(ዲያቆን)፡፡አበው ምን ይላሉ?፡፡
           (1999)አሳታሚና አከፋፋይ ማህበረ ቅዱሳን፣ቦታ አልተጠቀሰም፡፡)
      በእርግጥም ወንጌል የመሰከረለት በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የተዘረጋው መሰላል ክርስቶስ ነው፡፡(ዮሐ.1÷52)ክርስቶስ መካከለኛ የሆነው ሰው ሆኖ ፤ደሙን አፍስሶ በሠራልን የቤዛነቱ ሥራ ነው፡፡ክርስቶስ በፍጹም ሰውነቱ እኛን ፤በፍጹም አምላክነቱ ደግሞ እግዚአብሔርን ወክሎ ሁለታችንን ያቀራረበ መካከለኛ አማኑኤል ነው፡፡እርሱወደአባቱ ለመድረስ ጐዳና ፤ወደወለደው ለመግባት የሚሆን በርነው፡፡ጎዳናው ልክ እንደመሰላሉ ከምድር እስከሰማይ የሚደርስና የቀናም ነው፡፡በዚህ መካከለኛነቱምየአብ ሊቀ ካህናት የሚሆን እርሱ የሰውን ባህርይ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀ፡፡”(መጽሐፈ ቅዳሴ ጕልህ፡፡(1994)፡፡አዲስ አበባ፣ትንሳኤ ማተሚያ ድርጅት፡፡ገጽ 146፤የቅዳሴ ሥርዐት ገጽ.82)


Saturday, 25 January 2014

ነፃ አወጣን


በራሣችን ፈርደን የሞት ኑሮ ስንኖር፤
በመንፈሰ ደይን ባርያዎች ተብለን፤
በኃጢአት ጭቅቅት ጠረናችን ጠፍቶ፤
የነፍስ ገላዋ በዕድፈት ተበላሽቶ፤
ያልፈጠረን ጌታ በዕዳ ጽህፈት፤

Tuesday, 21 January 2014

የኢየሱስ ደም - ክፍል ስድስት

    Read in PDF:
    6- ደሙ ከኃጢአታችን ሁሉ ያነጻናል፡፡

“የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።” (1ዮሐ.1÷7)

“… እርሱም የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው፥ ለኃጢአታችንም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ ኃጢአት እንጂ።” (1ዮሐ.2÷2)

“… እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው፥ ልብሳቸውንም አጥበው በበጉ ደም አነጹ።” (ራዕ.7÷14)

“በአንድ ልጁ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ከኃጢአታችን መዳንን የሰጠን ፤የሁሉ ህይወት ወደእርሱ የሚሸሹትን የሚረዳ ወደእርሱ ለሚጮኹ ሰዎች ተስፋቸው፡፡” (የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ)

“ጥበብ ግን መድኃኒታችን ነው በሥጋው መሥዋዕትነት ያዳነን በደሙም ፈሳሽነት የተወዳጀን ለመንግስቱም የመረጠን...”(የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ)
       ጌታ በመዋዕለ ሥጋዌው ከአይሁድ የገጠመው ዋናውና ትልቁ ተቃውሞ ኃጢአትን ይቅር ስለማለቱ ነው፡፡(ማር.2÷6)በእርግጥም ኃጢአትን ይቅር ማለት የሚቻለው አምላካዊነት ባህርይ ያለው አካል ብቻ ነው፡፡አይሁድ በዚህ ምክንያት ኢየሱስን እስከሞት ጠሉት፡፡ክርስቶስ ኃጢአትን ይቅር የማለት ሥልጣን እንዳለው በግልጥ አሳይቷል፡፡ይህ ግን ለአይሁድ እግዚአብሔርን እንደመናቅ ያለ ታላቅ ስድብ ነበር፡፡ለዚህም ነው ሉቃስ በወንጌሉ “ … ነገር ግን በምድር ላይ ኃጢአት ሊያስተሰርይ ለሰው ልጅ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ ብሎ … ” በማለት በግልጥ የፃፈልን፡፡(ሉቃ.5÷24)

Friday, 17 January 2014

ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ፡፡(ማቴ.3÷8)

Read in PDF

የስሙ ትርጓሜ “እግዚአብሔር ፀጋ ነው” ማለት ነው፤የተወለደው “በጌታ ትዕዛዝ ህግጋት ሁሉ ያለነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ከነበሩት” ከቅድስት ኤልሳቤጥና ከካህኑ ዘካርያስ ነው፡፡(ሉቃ.1÷6)፡፡ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ኃጢአትን ያልሰሩ ጻድቃን አልነበሩም ነገር ግን የእግዚአብሔርን ህግና ሥርዓት በማክበር ታማኞችና እጅግም ቅኖች ነበሩ፡፡የእግዚአብሔር ቅዱሳን ህይወታቸውን በንስሐ ያጠሩ ብቻ ሳይሆኑ ፤ንስሐቸውም ፍሬ የሚያፈራና የሚታይ ህይወት የሚነበብበት ነው፡፡ኤልሳቤጥና ዘካርያስ ህይወታቸው በእግዚአብሔር ፊት ያለነቀፋ የሆነውን ያህል በሰውም ፊት ነውር ያልነበረባቸው ነበሩ፡፡
     በሌላ ንግግር ኤልሳቤጥና ዘካርያስ ስም ብቻ ያልነበራቸውና ያልከበዳቸው አማኞች ነበሩ፡፡ለታመኑለት ጌታ የሚታመንና በፍሬ የሚታይ ህይወት ነበራቸው፡፡ዛሬ ክርስትናችንን ከሚያስነቅፉብን ነገሮች ዋነኛውና ትልቁ “ክርስቲያን የሚለው ስም አለን ነገር ግን ስሙ በእኛ የማይሰራ ሙትመሆኑ ነው፡፡(ራዕ.3÷1)፡፡ክርስቲያን ተብሎ የሚጠራው ጥቂት የማይባለው ማህበረሰብ የነጠላ ያህል በነውር ካጌጠ ፣የላንቃ ያህል በዝሙት ከተቆነጀ፣በጉበኝነት ከተሞሸረ፣አለልክ በማግበስበስና በስግብግብነት ከተካነ …  ዘመን ቆጥሮብናል፡፡

Wednesday, 15 January 2014

አድጎ ያፈራ 'ለት


ሳንጀምረው ፈርተን
ሳንቀርበው ርቀን
ሳንሻገር ቆመን
እሾሁን መንጥረን
ኩርንችቱን ነቅለን
ካ'ንድም ሁለት ሶስቴ ሳንጎለጉል ደክመን
እርፍና ሞፈሩን ቀንበርም አጣምደን
የእርሻና የዘር ወራቱን ታግሰን
ብናርስ ብንኰተኩት
በዓላማ በጽናት፤

Sunday, 12 January 2014

ነጻነትን ለኃጢአት?

ከበለዐም መርገም አስማትና ምዋርት
ከባላቅም ምክር ቃየላዊ ክፋት
እስራኤል አምልጧል ከበዛው ተግዳሮት
ቀስቱ ተቀንጥሶ ወጥመድ ተሰብሮለት፡፡
           ተሽሯል እርግማን ኃይል አጥቷል አስማቱ
           የሠራዊት ጌታ ጣልቃ በመግባቱ
           በአህያ አንደበት የታላቁ ነቢይ ታግዶ እብደቱ፡፡

Wednesday, 8 January 2014

የኢየሱስ ደም (ክፍል - አምስት)



3-ደሙ የተዋጀንበት ዋጋችን ነው፡፡

              “በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን፥ ነውርና እድፍ እንደሌለው እንደ
               በግ ደም በክቡር የክርስቶስ ደም እንደ ተዋጃችሁ ታውቃላችሁ።
                   (1ጴጥ.1÷19)
      “ዋጀየሚለውን መዝገበ ቃላቱገዛ፣ካሳከፈለ (ከሞት፣ ከባርነትለማዳን)፣አዳነብሎ ይፈታዋል፤ (ኣማርኛ መዝገበ ቃላት፡፡(2001)፤ አዲስ አበባ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ማተሚያ ቤት፡፡ገጽ.426) ውጅት ማለት ቀድሞ የራስ የነበረን ንብረት በኋላ ግን ከዋናው ባለቤት ወጥቶ ወደሦስተኛ አካል የገባን ዋጋ ያለውን ሀብት የሚያስፈልገውን ሁሉ ቅጣት በመቀበልና ዕዳውን በመክፈል ነጻ ማውጣትና የራስ ማድረግ ማለት ነው፡፡በዚህ አገባብ ከጥንት የእግዚአብሔር የነበረው ታላቁ ሀብት የሰው ልጅ በገዛ ነጻ ፈቃዱ ወደዲያብሎስ ፈቀቅ በማለቱ ክርስቶስ ኢየሱስ ሰው ከእግዚአብሔር ፈቀቅ በማለቱና ኃጢአት ሠርቶ ሊቀበል የሚገባውን መራራ መከራና ሞት (ቅጣቱን) ተቀብሎ፤ዕዳውን ሁሉ በመክፈል በገዛ ደሙ የሰውን ልጅ ገዛው፡፡
     የተዋጀነው በቀዳሚነትከሕግ እርግማንነው፤ (ገላ.3÷13) እርሱ ስለእኛ የተረገመ ሆኖ እኛን በሕጉ ከመረገምና ሕግን ባለመፈጸም ከሚመጣብን የሞት እርግማን ዋጀን፡፡ እርግማናችን ሁሉ በመስቀሉ ተጠርቆ ከመንገድ ተወግዷልና አሁን እኛ በመስቀሉ ሥራ፤ በክርስቶስ ሞትና በደሙ ተዋጅተን ንጹሐን ሆነናል፡፡ በቀጣይነት የተዋጀነውከአመጽ ሁሉነው፤ (ቲቶ.2÷14) በሐዲስ ኪዳን ጸሐፍት ኃጢአት ሁሉ አመጽ ነው፤ (1ዮሐ.5÷17) ክብር ይግባውና ከእንዲሁ ምህረቱ የተነሳ መድኃኒታችን በመድኃኒት ደሙ አዳነን፡፡

Sunday, 5 January 2014

ድንግል ፈጣሪዋን ወለደች፡፡(ቅዱስ ቄርሎስ)

በእግዚአብሔር መንግስት ታሪክ እጅግ ልዩና ታላቅ የሆነ ምስጢር ነው፤የአካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ሥጋን ነስቶ የባህርያችን መመኪያ ሆኖ መገለጡ፡፡ነቢያት ለብዙ ሺህ አመታት የናፈቁት ፣ትንቢት ተንብየው ሱባዔ ቆጥረው ከሩቅ ያዩት ፣አባቶችና እናቶች በራዕይና በምሳሌ የተረዱት … እውነተኛው ጌታና አምላክ ፣ህጻንና ልዑል የእኛን ሥጋ ለብሶ እንዲህ  ተገለጠ፡፡
    ከነቢየ እግዚአብሔር ከሚልኪያስ ወዲህ የእግዚአብሔር ራዕይና ትንቢት እነሆ በግልጥ መገለጥ ከተወና ዝም ካለ፤ዘመኑም የዝምታ ዘመን ከተባለ እነሆ አራት መቶ አመታት አልፈዋል፡፡የምሳሌው አገልግሎት በሚገለገልበት በዚያ በጨለማ ዘመን ላይ የእግዚአብሔር ዝምታ ሲታከልበት ምን ያህል እጅጉን ይከፋ ይሆን? …የመከራው ዘመን ዕለቱ ዓመት …ዓመቱ ዘመን ይሆናል፤መከራ አሻጋሪው እግዚአብሔር ደግሞ ሲለየው መከራው ክብር አልባ ብቻ አለመሆኑ ሳይሆን ከሞት ይልቅ የሚከብድ ይሆናል፡፡“ሊነጋጋ ሲል አብዝቶ ይጨልማል ”እንዲሉ የብርሃንና የምህረት ዘመንን ጌታ ሊያመጣ ኋላው አብዝቶ ድቅድቅ፤አብዝቶ ዳፍንት ጨለማ ሆነ፡፡

Friday, 3 January 2014

ጸሎት - ሰባራ በግህን አትለፈኝ!!!

ሁለንተናህ ቅዱስ ዘወትር የምትናፈቅ ፤ማለዳህ ጽድቅ ሠርክህም ምህረት የሆንከው ጌታዬ! ሰባራው በግህ እኔን የተሸከምከኝ ውዱ እረኛዬ ሆይ አመሰግንሐለሁ፡፡ጠባቂዬ! በሚያልፍና በማይጠቅመው ሸክላ ማንነቴ ተመክቼ ያንተን እረኝነትና መጋቢነት ንቄ ብሔድ እንኳ ከፊቴ ቀድመህ የማርፍበትን ለምለም መስክ የምረካበትንም የዕረፍት ውኃን አዘጋጅተህልኛልና አመሰግንሐለሁ፡፡
   
መልካሙ እረኛዬ ኢየሱስ ሆይ! እኔ ሰባራህ በግህ ነኝ፡፡በቤትህ በፀጋህ እንዳደጉትና እንደጐለመሱት የማልበረታ ታናሽና ኃጢአተኛ ብላቴናህ ነኝ፡፡ሰው እንደማትንቅ ፣ሰባራ በግ እኔን ልጅህን አይተህ እንደማታልፍየጤሜዎስ ልጅ በርጠሜዎስን ፣ቀራጩ ሌዊን ፣ሰባት አጋንንት የወጡላት የመግደሎሟን ሴት ማርያምን ፣መዳን የሆነለት ዘኬዎስን፣ሰው የሌለው የቤተ ሳይዳ መጻጉዕን፣ባለንዳድዋንና ደካማዋን የኬፋን አማት ፣አለማመኑን የረዳህለትን ሽባእኔን አመንዝራና አመጸኛ ባርያህንም ስትሰበስብ አይኔ አይታሀለችና ነፍሴ ትመካብሐለች፡፡