የእስራኤልን ወደ ባቢሎን መማረክ፣ ፊት
ለፊት ከተናገሩት ነቢያት መካከል ቀዳሚው ነቢዩ ኤርምያስ ነው። ነቢዩ ዘመኑን በእንባና በልቅሶ ያሳለፈና አብዝቶ ከማልቀሱም
የተነሣ “አልቃሻው ነቢይ” የሚል ቅጽል ስም የተሰጠው ነው። የኤርምያስ ዘመኑ ብቻ ሳይኾን ሕይወቱም ጭምር አሳዛኝና በሕመም፤ በሰቆቃ
የተሞላ ነበር።
Wednesday 16 October 2024
ኤርምያስ፤ ፍርድና ተስፋን ተናጋሪ ነቢይ!
Wednesday 9 October 2024
Saturday 5 October 2024
Friday 4 October 2024
“አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ” (ማቴ. 16፥16)
ጌታችን ኢየሱስ፣ በምድርም ኾነ በሰማይ ካለ ከየትኛውም ፍጡር፣ ባህልና ልምምድ፤ ከየትኛውም የዓለም ሥርዓትና አስተዳደር ጋር አይወዳደርም! ቅዱስ ጴጥሮስ ይህን በማስተዋል ነው፣ የተገለጠለትን እውነት የመሰከረው። ይህ ቅዱስ ምስክርነት፣ ክርስትና ተንጣልሎ የተመሠረተበት ሕያውና ዘላለማዊ መሠረት ነው። የቤተ ክርስቲያን ሕይወት፣ ተልእኮ፣ ታላቅ ተስፋና ዘላለማዊነት የተወሰነውና የሚጸናው፣ ይህን ታላቅ ምስክርነት በመቀበልና በማመን ብቻ ነው።
Thursday 3 October 2024
“ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ” (ፊል. 4፥4)
የፊልጵስዩስ ቤተ ክርስቲያን፣ በኹለተኛው የቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያዊ አገልግሎት የተወለደች ቤተ ክርስቲያን ናት። ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ኹለተኛው ሐዋርያዊው ጉዞው፣ ብዙ መከራና እንግልትን ተቀብሎአል። የመጀመሪያው ሐዋርያዊው ጉዞው ብዙ መከራ የሌለበትና ቀለል ያለ ነበር፤ ኹለተኛው ግን ጠንካራና በብዙ መገፋት ውስጥ ያለፈበት ነው።
Sunday 29 September 2024
ኢየሱስ “ከሃይማኖተኝነት” ይበልጣል!
"... ወደ የትኛውም ሃይማኖት ዛሬ ተነስታችኹ ለመግባት ትችላላችሁ።
ጴንጤ ለመኾን ግን መመረጥ ያስፈልጋል" (በጋሻው ደሳለኝ)
“ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል
ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።” (ኢየሱስ ክርስቶስ - ዮሐ. 10፥16)
Saturday 28 September 2024
Monday 23 September 2024
የቤተ ክርስቲያን ሌላኛው ተግዳሮት!
የትምህርትም፤ የምግባርም ውድቀት፣ የቤተ ክርስቲያንን ኹለንተናዊ መልክ
ከሚያበላሹ መካከል ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛሉ። ትምህርቱ እንደ ኑፋቄ ያለ ሲኾን፣ ምግባራዊ ውድቀቱ ደግሞ እንደ ሰዶማዊነትና
ዓለማዊነት ያሉ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሲከሰቱ እጅግ ጆሮን ጭው ያደርጋሉ። እኒህን ተግባራት የሚፈጽሙ ሰዎች አንዳንድ[?] በ“ሃይማኖት”
ጥላ ሥር ያሉ ሰዎች ስለ መኾናቸው ብዙዎቻን እማኝ ነን።
Thursday 19 September 2024
Saturday 14 September 2024
ዘነበ ወላ(ጋሽ)ና ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ!
ዘነበ ወላ፣ ሰሞኑን ሥራና ምናኔን አስመልክቶ የሰጠው አስተያየት በብዙ ኦርቶዶክሳውያን ዘንድ ጥርስ አስነክሶበታል። ብዙ ኦርቶዶክሳውያን የሰላ ትችት ሲሰነዘርባቸው፣ ችግሮቻቸውንና ስህተቶቻቸውን ከማረቅ ይልቅ፣ ቤተ ክርስቲያንን ለማዋረድ የሚነገር አድርጎ ማሰብ፣ “ልጅ እናቷን ምጥ አታስተምርም” የሚል አጉል ፈሊጥ መጥቀስ፣ ዛሬ መጥታችኹ ቤተ ክርስቲያንን ወንጌል ልትሰብኳት፣ ችግሯን ልታመለክቱ አትችሉም … የሚሉ አያሌ አሉታዊ ምላሾች ይቀርባሉ። ይህን ስንል ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማዋረድ የሚሠሩ የሉም ማለት አልችልም። ይኹንና ደግመን ደጋግመን መናገር የምንፈልገው፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ ወደ እውነተኛ የወንጌል ጐዳና እስክትመለስና በመካከልዋ ያለውን “ዕድፍና ጉድፍ” እስክታስወግድ ድረስ “የተሐድሶ ድምጽ” ማሰማታችንን አናቆምም!
Wednesday 11 September 2024
ዘመን የተጨመረልን በመግቦቱ ነው!
የእግዚአብሔር መግቦት እጅግ አስደናቂ ነው። ጌታ ፍጹም መጋቢ ስለ ኾነ
በፍጥረት መካከል አድልዎ ሳያደርግ የሚተገብራቸው አያሌ መግቦቶች አሉ፤ ቅዱሳት መጻሕፍትን ዋቢ አድርገን ምሳሌ ብንጠቅስ፦ “ርሱ[እግዚአብሔር] በክፎዎችና በበጎዎች
ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።” (ማቴ. 5፥44)፣ እንዲኹም እግዚአብሔር አምላክ ጋብቻን ባርኮ
ለመላለሙ በአምላካዊ መግቦቱ መስጠቱን እናስተውላለን፤ (ዘፍ. 2፥24፤ ማቴ. 19፥4-5)።
Tuesday 10 September 2024
Wednesday 4 September 2024
የቁባቱን በድን የቆራጠው ካህን! (መሳ. 19-20)
በእስራኤል ልጆች ታሪክ ውስጥ አያሌ አስከፊ ተግባራት ተከናውነዋል፤ ዛሬ
የምናየው ይህ አንዱ ነው፤ “በዚያም
ዘመን በእስራኤል ዘንድ ንጉሥ በሌለበት ጊዜ በተራራማው በኤፍሬም አገር ማዶ የተቀመጠ ሌዋዊ ነበረ፤” (መሳ. 19፥1) ይላል፣ በመሳፍንት
መጽሐፍ ውስጥ ከተቀመጡት የብንያም ሰዎችን የሥነ ምግባር ብልሹነትና በምላጭ ጫፍ ላይ መቆማቸውን ከሚያሳዩት ታሪኮች አንዱን
ለመተረክ ሲነሳ።
በርግጥ ሌዋዊው ካህን ቁባቱን ፍለጋ ከኤፍሬም ወደ ቤተልሔም መሄዱ፣ ከአንድ
ሚስት በላይ ማግባቱን ያሳያል፤ ይህ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት ያለው ተግባር አልነበረም፤ በተጨማሪም፣ እግዚአብሔር
ለእስራኤል ልጆች መሳፍንትን የሰጠው፣ ርሱ ብቻውን በነርሱ ላይ ሊነግሥ ነበር። ነገር ግን ለጌታ ከመታዘዝ ይልቅ፣ የሃይማኖት
መሪዎቿ ድካምና ኃጢአት እያየለባቸውና እየባሰባቸው ሲሄድ በተደጋጋሚ እንመለከታለን።