Friday 4 October 2024

“አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ” (ማቴ. 16፥16)

Please read in PDF

ጌታችን ኢየሱስ፣ በምድርም ኾነ በሰማይ ካለ ከየትኛውም ፍጡር፣ ባህልና ልምምድ፤ ከየትኛውም የዓለም ሥርዓትና አስተዳደር ጋር አይወዳደርም! ቅዱስ ጴጥሮስ ይህን በማስተዋል ነው፣ የተገለጠለትን እውነት የመሰከረው። ይህ ቅዱስ ምስክርነት፣ ክርስትና ተንጣልሎ የተመሠረተበት ሕያውና ዘላለማዊ መሠረት ነው። የቤተ ክርስቲያን ሕይወት፣ ተልእኮ፣ ታላቅ ተስፋና ዘላለማዊነት የተወሰነውና የሚጸናው፣ ይህን ታላቅ ምስክርነት በመቀበልና በማመን ብቻ ነው።

Thursday 3 October 2024

“ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ” (ፊል. 4፥4)

 Please read in PDF

የፊልጵስዩስ ቤተ ክርስቲያን፣ በኹለተኛው የቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያዊ አገልግሎት የተወለደች ቤተ ክርስቲያን ናት። ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ኹለተኛው ሐዋርያዊው ጉዞው፣ ብዙ መከራና እንግልትን ተቀብሎአል። የመጀመሪያው ሐዋርያዊው ጉዞው ብዙ መከራ የሌለበትና ቀለል ያለ ነበር፤ ኹለተኛው ግን ጠንካራና በብዙ መገፋት ውስጥ ያለፈበት ነው።

Sunday 29 September 2024

ኢየሱስ “ከሃይማኖተኝነት” ይበልጣል!

"... ወደ የትኛውም ሃይማኖት ዛሬ ተነስታችኹ ለመግባት ትችላላችሁ። ጴንጤ ለመኾን ግን መመረጥ ያስፈልጋል" (በጋሻው ደሳለኝ)

“ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።” (ኢየሱስ ክርስቶስ - ዮሐ. 10፥16)

Monday 23 September 2024

የቤተ ክርስቲያን ሌላኛው ተግዳሮት!

 Please read in PDF

የትምህርትም፤ የምግባርም ውድቀት፣ የቤተ ክርስቲያንን ኹለንተናዊ መልክ ከሚያበላሹ መካከል ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛሉ። ትምህርቱ እንደ ኑፋቄ ያለ ሲኾን፣ ምግባራዊ ውድቀቱ ደግሞ እንደ ሰዶማዊነትና ዓለማዊነት ያሉ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሲከሰቱ እጅግ ጆሮን ጭው ያደርጋሉ። እኒህን ተግባራት የሚፈጽሙ ሰዎች አንዳንድ[?] በ“ሃይማኖት” ጥላ ሥር ያሉ ሰዎች ስለ መኾናቸው ብዙዎቻን እማኝ ነን።

Saturday 14 September 2024

ዘነበ ወላ(ጋሽ)ና ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ!

Please read in PDF

ዘነበ ወላ፣ ሰሞኑን ሥራና ምናኔን አስመልክቶ የሰጠው አስተያየት በብዙ ኦርቶዶክሳውያን ዘንድ ጥርስ አስነክሶበታል። ብዙ ኦርቶዶክሳውያን የሰላ ትችት ሲሰነዘርባቸው፣ ችግሮቻቸውንና ስህተቶቻቸውን ከማረቅ ይልቅ፣ ቤተ ክርስቲያንን ለማዋረድ የሚነገር አድርጎ ማሰብ፣ “ልጅ እናቷን ምጥ አታስተምርም” የሚል አጉል ፈሊጥ መጥቀስ፣ ዛሬ መጥታችኹ ቤተ ክርስቲያንን ወንጌል ልትሰብኳት፣ ችግሯን ልታመለክቱ አትችሉም … የሚሉ አያሌ አሉታዊ ምላሾች ይቀርባሉ። ይህን ስንል ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማዋረድ የሚሠሩ የሉም ማለት አልችልም። ይኹንና ደግመን ደጋግመን መናገር የምንፈልገው፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ ወደ እውነተኛ የወንጌል ጐዳና እስክትመለስና በመካከልዋ ያለውን “ዕድፍና ጉድፍ” እስክታስወግድ ድረስ “የተሐድሶ ድምጽ” ማሰማታችንን አናቆምም!

Wednesday 11 September 2024

ዘመን የተጨመረልን በመግቦቱ ነው!

 Please read in PDF

የእግዚአብሔር መግቦት እጅግ አስደናቂ ነው። ጌታ ፍጹም መጋቢ ስለ ኾነ በፍጥረት መካከል አድልዎ ሳያደርግ የሚተገብራቸው አያሌ መግቦቶች አሉ፤ ቅዱሳት መጻሕፍትን ዋቢ አድርገን ምሳሌ ብንጠቅስ፦ “ርሱ[እግዚአብሔር] በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።” (ማቴ. 5፥44)፣ እንዲኹም እግዚአብሔር አምላክ ጋብቻን ባርኮ ለመላለሙ በአምላካዊ መግቦቱ መስጠቱን እናስተውላለን፤ (ዘፍ. 2፥24፤ ማቴ. 19፥4-5)።

Wednesday 4 September 2024

የቁባቱን በድን የቆራጠው ካህን! (መሳ. 19-20)

 Please read in PDF

በእስራኤል ልጆች ታሪክ ውስጥ አያሌ አስከፊ ተግባራት ተከናውነዋል፤ ዛሬ የምናየው ይህ አንዱ ነው፤ “በዚያም ዘመን በእስራኤል ዘንድ ንጉሥ በሌለበት ጊዜ በተራራማው በኤፍሬም አገር ማዶ የተቀመጠ ሌዋዊ ነበረ፤” (መሳ. 19፥1) ይላል፣ በመሳፍንት መጽሐፍ ውስጥ ከተቀመጡት የብንያም ሰዎችን የሥነ ምግባር ብልሹነትና በምላጭ ጫፍ ላይ መቆማቸውን ከሚያሳዩት ታሪኮች አንዱን ለመተረክ ሲነሳ።

በርግጥ ሌዋዊው ካህን ቁባቱን ፍለጋ ከኤፍሬም ወደ ቤተልሔም መሄዱ፣ ከአንድ ሚስት በላይ ማግባቱን ያሳያል፤ ይህ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት ያለው ተግባር አልነበረም፤ በተጨማሪም፣ እግዚአብሔር ለእስራኤል ልጆች መሳፍንትን የሰጠው፣ ርሱ ብቻውን በነርሱ ላይ ሊነግሥ ነበር። ነገር ግን ለጌታ ከመታዘዝ ይልቅ፣ የሃይማኖት መሪዎቿ ድካምና ኃጢአት እያየለባቸውና እየባሰባቸው ሲሄድ በተደጋጋሚ እንመለከታለን።

Saturday 31 August 2024

“ኑ ወደ ኦርቶዶክስ ተመለሱ!” ለምትሉን!

 Please read in PDF

ኦርቶዶክሳዊው ተሐድሶ እያየለና በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነትን እያገኘ ሲመጣ፣ በቃላት በማባበል፣ በጥቅምና በክብር በማማለል፣ መልሰን አናወግዛችሁም በሚል የተስፋ ቃል በመስጠት … እየቀረበልን ያለው ጥያቄ፣ “ኑ! ወደ ኦርቶዶክስ ተመለሱ!” ሚል ነው። ከዚህ በታች የምናስቀምጣቸው ጠንካራ ምክንያቶች የመመለስና ያለ መመለስን ጥያቄ ትርጕም ይሰጡታል።

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ወደ ኋላ ስለ መመለስ በማስጠንቀቂያ አዘል ከተጻፉ መልእክቶች አንዱ፣ የዕብራውያን መልእክት ነው። የሐዋርያት ሥራን መጽሐፍ ስናጠና እንደምናስተውለው፣ አስቀድሞ ክርስትናን ለተቀበሉ አይሁድ የመጀመሪያዎቹ የቤተ ክርስቲያን ዓመታት እጅግ አስቸጋሪዎች ነበሩ። በእነዚህ ጊዜያት ክርስትና በአጭሩ የአይሁድ ሃይማኖት ኾኖ ነበር። ከ120ው የጌታ ቤተ ሰቦች (ሐ.ሥ. 1፥15) ጀምሮ ኹሉም በአንድነት ያመልኩና ያገለግሉ የነበረውም በአይሁድ ቤተ መቅደስ ውስጥ ነበርና፤ (ሐ.ሥ. 2፥46፤ 3፥1፤ 5፥42)።