4. እውነት አንጻራዊ ናት፦ በአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አስተምህሮ መሠረት ፍጹም እውነት የለም፤ ምክንያቱም ኹሉም እምነቶች ትክክልና ትክክለኛ ናቸው። ለምሳሌ፦ በክርስትና አስተምኅሮ አንድ ሰው ከጋብቻ ውጭ የሚያደርገው ማናቸውም ሥነ ምግባራዊ ርኩሰት አመንዝራነት ነው፤ ለአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ግን ርኩሰት ሳይኾን ትክክል ነው። በጋብቻ ውስጥም፤ ከጋብቻ ውጭም የሚደረግ አመንዝራት እውነትና ውሸት ቢኾንም፣ ለነርሱ ግን ኹለቱም እውነት ነው።
Wednesday, 12 November 2025
Friday, 7 November 2025
ቤን ሂንና ኑፋቄው!
ሰውየው አስቀድሞ መጠሪያው “Faith World Church - የእምነት ዓለም ቤተክርስቲያን” በተባለ፣ በአኹን ወቅት
ደግሞ “World Healing Center Church - የዓለም የፈውስ ማዕከል ቤተክርስቲያን” የሚል ስያሜ የተሰጠው የግል “ቤተ ክርስቲያን” ያለውና “የብልጽግና
ወንጌልን” አቀንቃኝ “ንጥጥ ባለጠጋ” ነው። ከባለጠግነቱና ከቅምጥልነቱ የተነሣ፣ የሂን የወንድም ልጅ የኾነው
ፓስተር ኮስቲ ሂን በርሱ ቤት ተጠልሎ ሳለ ያየውን ሲናገር፣ ቅዱስ ጳውሎስና
እነርሱ የሚለያዩበትን አንድ እውነት፣ “እኛ የጳውሎስን አይነት ወንጌል አንሰብክም ነበር።” በማለት ገልጦታል።[1]
በምስክርነቱ ላይ ኮስቲ ሂን፣ እሱ እና ቤተሰቡ የያዙትን ውድ መኪናዎች እና ውድ ቤቶችን እና በጉዞው ዙሪያ ስላለው የቅንጦት ኹኔታ
ገልጦአል።[2]
ኮስቲ ሂን የአጎቱን የብልጽግና ወንጌል እና አስተምህሮ በመተቸት ብዙዎቹ ትንቢቶቹ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር እንደሚቃረኑ ጽፎአል።[3]
Tuesday, 4 November 2025
ቃሉን የሚያነብብ ብፁዕ ነው!
ቅዱስ ቃሉን ማንበብ መንፈሳዊና ታላቅ አምልኮ ነው፤ አቡቀለምሲሱ ቅዱስ ዮሐንስ፣ “[ቅዱስ ቃሉን] የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።” (ራእ. 1፥3) ይለናል። ሐዳሲው ቅዱስ ዕዝራ፣ “... ወንዶችና ሴቶች የሚያስተውሉም ሲሰሙ፥ ከማለዳ ጀምሮ እስከ ቀትር ድረስ አነበበው የሕዝቡም ሁሉ ጆሮ የሕጉን መጽሐፍ ለመስማት ያደምጥ ነበር።” (ነህ. 8፥3) እንዲል፣ ቃሉን ከእኩለ ቀን በላይ ማንበብ እጅግ ታላቅ አምልኮ ነው።
Friday, 24 October 2025
የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፮
3. ክርስቶስ የመዳን ራስ እንደ ኾነ የሚታመነውን የክርስትና ዋና እምነት ጨርሰው ይክዳሉ፦ በአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ
አስተምኅሮ መሠረት፣ ኢየሱስ ክርስቶስ አንድ “ዮጊ” ወይም “የዕውቀት ብርሃን ያገኘ የበራለት ሰው ብቻ” ነው። ይህም ብቻ ሳይኾን፣
ርሱን ፍጹም አምላክ ነው ብሎ ማመንና ማምለክ፣ መጥፎና ሰዎችን ‘እውነተኛ ኃይላቸውን’ ከማወቅ ለማራቅ የታለመ የውሸት ትምህርት
ነው ብለው ያምናሉ፤ ያስተምራሉም።
Thursday, 16 October 2025
የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፭
በባለፈው ክፍል እንደ ተመለከትነው፣ የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አስተማሪዎች፣ የመጽሐፍ ቅዱስን
ሥልጣንን ጨርሶ እንደማይቀበሉና እንደሚያቃልሉ አንስተናል፤ በዚሁ ዐሳብ ላይ ጥቂት እንጨምርና ወደሚቀጥለው እንሄዳለን።
የጽድቅ መንፈስ የኾነው መንፈስ ቅዱስ ወደ ጽድቅና ቅድስና የሚመራና ደግሞም እርሱ የቅዱስ ቃሉ
ባለቤትና ደራሲ ነው፤ ስለዚህም ቅዱስ ቃሉ የሕይወታችን፣ የአምልኮአችን፣ የአገልግሎታችን፣ የአስተምኅሮና የምልልሳችን ኹሉ ማዕከልና
ቃኚ ነው። ቃሉን በመንፈስ ቅዱስ አብርሆት በትክክል ሳንረዳ ተሳስተን ብንወድቅ፣ እኛ እንጎዳለን እንጂ ቃሉ እውነተኛና የታመነ
ነው። “ባናምነው፥ እርሱ የታመነ ሆኖ ይኖራል፤ ራሱን ሊክድ አይችልምና።” እንዲል (2ጢሞ. 2፥13)።
Sunday, 12 October 2025
የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፬
አስቀድመን እንደ ተናገርነው፣ “ኒው ኤጅ ሙቭመንት”[1] አዲስ “እምነት” እንደሚመስል ስያሜው ቢናገርም፣ ነገር ግን
ትምህርቱ፣ ከኖስቲዝም፣ ከክርስትና ከሂንዱና ከሌሎችም ቤተ እምነቶች የተቀዳና የተለቃቀመ ትምህርት ነው።[2] ከክርስትና በቀዳው አመለካከቱ ስለ እምነት የሚናገር ቢመስልም፣
ዕውቀትን በማምለክ ደግሞ ኖስቲዝምን “ቁርጥ ነው”፤ በልምምዶቹ ከጥንቁልና ጋር ቢመሳሰልም፣ ክርስቲያኖችን ለመምሰል ግን ከመጽሐፍ
ቅዱስ በመጥቀስ ደግሞ “የሰይጣንን ብርሃናዊ መልክ” ለመያዝ ይጥራል!
Saturday, 27 September 2025
የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፫
በባለፉት ክፍሎች ግቦቻቸውንና ዋና ዋና አስተምኅሮአቸውን ማየታችንን
እያስታወስን ዛሬም ቀጣዩን ዋና ዋና አስተምኅሮአቸውን እናነሳለን። የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አማኞች፦
3. ክርስቶስ አንድ “ዮጊ” ነው፤ ነገር ግን ከርሱም የሚበልጡና
የላቀ መገለጥ ያላቸው “ዮጊዎች” እንዳሉ ያምናሉ። ኢየሱስ ብሩህ አስተማሪ ነበር፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ልጅ አልነበረም በማለት
ያስተማራሉ። ከዚሁ ጋ በተያያዘ የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አማኙና አስተማሪው ኤልያስ ገብሩ(ዶ/ር) የተባለ ሰው፣ ራሱን ከእግዚአብሔር
ለማስተካከልና ኹሉም ነገር በውስጡ እንዳለ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች “ቦጫጭቆ በመስፋት” እንዲህ ይላል፣
Friday, 26 September 2025
መስቃላና መስቀል ምን አገናኛቸው?
ዋቄፈታ ዋቃ ከሰማይ
አውርዶልናል ብሎ ከሚያምናቸው አያሌ በአላት መካከል አንዱ የመስቀላ በአል ነው፤ ካልታተመው መጽሐፌ ዋቄፈታ ስለ መስቀላ የሚያምነውን
እንዲህ አስነብባችኋለሁ፤
“ … በአሉ በሌሎች ስፍራዎች፣ “ዳሞቲ” እየተባለ
ይጠራል።[1] “ሁሉቆ” ብለውም
የሚጠሩት አሉ፤[2] ችግሮችንና ክፉውን
መናፍስት ለማራቅ የጉባ ወይም የማቃጠል ሥርዓት ይከናወናል።[3]
ይህ
በአል “ጉባ” ተብሎ በሰሜን ሸዋ አከባቢ ነሐሴ 16 ቀን ይከበራል። በአብዛኛው ቦታ
ደግሞ ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የ“መስቀል” ክብረ በአል ጋር ተያይዞ የሚከበር ነው።
Tuesday, 23 September 2025
የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፪
የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አንድና ወጥ የኾነ የእምነት አቋም ወይም መርሕ የለውም። ነገር
ግን ከክርስትና፣ ከምሥራቃዊ ምስጢራዊነት፣ ሂንዱይዝም፣ ቡሂድዝም፣ ሜታፊዚክስ፣ ተፈጥሮአዊነት፣ ኰከብ ቈጠራ፣ አስማት ወይም ጥንቆላን
እና ከሳይንሳዊ ልቦለድ የተውጣጡ የተለያዩ ፅንሰ ዐሳቦችን እና ልምምዶችን በመጠቀም ወደ ሙሉ አቅም ለመድረስ መጣርን የሚያበረታታ
እንቅስቃሴ ነው። ኹሉም ቤተ እምነቶች ውስጥ ያለውን መልካም የተባሉትን ምግባራትና ልምምዶችን በመውሰድ የራሳቸው አድርገው ይጠቀማሉ።
Saturday, 20 September 2025
የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ (ክፍል - ፩)
ጥቅስ የጠቀሰ፤ መስቀል ያነገተ፤ ነጠላ ያመሳቀለ፤ አትሮንሱን ወይም ዓውደ ምሕረቱን ይዞ የሚሰብከው ኹሉ ሰባኪ ወይም የመጽሐፍ ቅዱስ አማኝ ስላለመኾኑ በዘመናችን አያሌ ምስክሮች አሉ። ጥቅሶች የሚጠቀሱት፤ ቅዱሳት መጻሕፍት የሚገለጡት ለእግዚአብሔር ክብር፣ ክርስቶስን ለማላቅ፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለማስፋት፣ የሰውን ኀጢአተኝነት ገልጠው ወደ እግዚአብሔር ጸጋ ለማቅረብ ... እንዳይደለ ከአደባባይ ያልተሠወረ ምስጢር እንደ ኾነ ሰነባብቶአል።
Tuesday, 9 September 2025
“የተሐድሶ ዋና ሰው ነበርኩ!” (ሰለሞን አቡበከር)
የምዩጣን ዐይን
ያወጣ ድፍረት!
ሰለሞን አቡበከርን በዝማሬዎቹ አውቀዋለኹ፤ ደጋግና ውዱድ መዝሙሮች አሉት፤ በትክክል ግን መዝሙሮቹን ርሱ ለመድረሱና ለመጻፉ እስክጠራጠር ድረስ “በሎዛ ሚዲያ” ያደረገውን ቃለ መጠይቁን ሰማኹት፤ በጣም በድፍረትና ባለማፈር ስለ ኦርቶዶክሳዊ ተሐድሶ አገልግሎት ሲናገርና የማያውቀውን ልክ እንደሚያውቅና ዋናው ሰው ርሱ እንደኾነ ሲናገር ሰምቼዋለኹ። ስለ ከንቱ ድፍረቱ ይህን አጭር ጽሑፍ መጣፍ ፈለግኹ!
Tuesday, 2 September 2025
በሰማይ ኢየሱስ በምድር ጰራቅሊጦስ አለን!
ቅዱስ ጳውሎስ ለሮም ቤተ ክርስቲያን በጻፈው መልእክቱ፣ በግልጥ ቃል፣ “እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም።” (ሮሜ 8፥1) በማለት፣ በክርስቶስ ላሉት ከእግዚአብሔር ዘንድ ዘላለማዊ ኵነኔ እንደማይጠብቃቸው ተናግሮአል፤ ክርስቶስ ስለ ሞተልን፤ ደግሞም ከሙታን መካከል ስለ ተነሣልን የኀጢአት ኃይል፤ የገሃነም ጉልበት የተሰበረልን የዳንን ሕዝቦች ነን።
Sunday, 31 August 2025
“ተሐድሶ ነን” ባይ የተሐድሶ ተግዳሮቶች!
ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ከክርስቶስ ትምህርት፣ ሕይወትና ሥራ አንጻር ተሐድሶ እንደሚያሻት ለጥያቄ የማይቀርብ ሐቅ ነው። በተደጋጋሚ ቤተ ክርስቲያኒቱ ራስዋ፣
“ተሐድሶ እንደሚያሻት” ስትናገር ሰምተናታል። ከዚኹ ጋር በተያያዘ፣ “ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማደስ” ከሚንቀሳቀሱ አካላት ሦስት ዓይነት
ተግዳሮቶች በግልጥ ይታያሉ፤
Wednesday, 27 August 2025
“ሄደህ …ስበክ”! (ዮና. 1፥1)
እግዚአብሔር አምላክ የተልእኮ አምላክ ነው። አስቀድሞ ሰው በኀጢአቱ በወደቀ ጊዜ ለማንሳት ወደ ወደቀበት ስፍራ፣ “ወዴት ነህ?” (ዘፍ. 3፥10) እያለ ፍለጋ የመጣው ያህዌ ኤሎሂም ነው። እግዚአብሔር ፍጥረት በወደቀ ጊዜ በመፈለጉና ፈልጎም በማግኘቱ፣ የተልእኮ አምላክ ነው። ርሱ ፍጥረት በመውደቁ ደስ አይሰኝም፤ “የምዋቹን ሞት አልፈቅድምና፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ስለዚህ ተመለሱና በሕይወት ኑሩ።” (ሕዝ. 18፥32) እንዲል።

.jpg)








