Sunday, 1 February 2026

እንቅልፋሙ ዮናስ!

 Please read in PDF

ወደ አሕዛባዊቷ ነነዌ የተላከው ዮናስ፣ ሕጋዊ ታሪፍ ከፍሎ ወደ ተርሴስ ኮበለለ። ቀለል አድርገን ካየነው፣ ዮናስ ሕጋዊ ክፍያ ፈጽሞ መሄዱ ችግር ላይኖርበት ይችላል፤ ነገር ግን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ አላደረሰውም። እንዲያውም የተሳሳተን ነገር በትክክለኛው መንገድ ለመሥራት መጣር ነገሩን ትክክል ካለማድረጉ ባሻገር አደገኛ ያለመታዘዝ ምልክት ነው። የእግዚአብሔርን ፈቃድና ትእዛዝ የሚቃረን ማናቸውም ነገር እጅግ ትክክል በተባለ መንገድ ቢደረግም ኀጢአት ነው። ይህ የዮናስ አደገኛ መንገድ ነው።



Sunday, 18 January 2026

ተጠመቀ ጌታ!

 Please read in PDF

ርደተ ገሃነም ርደተ መቃብር

በመርገመ ሥጋም የነፍስ ሲጨመር

ጽሕፈተ ዕዳችንም ደልቦ ወርዝቶ

Tuesday, 6 January 2026

አስፈሪው አምላክ በትህትና ንጉሥነቱ

 Please read in PDF

በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ለኪዳኑ ሕዝብ የተገለጠበት መንገድ እጅግ አስደናቂም፤ አስፈሪም ነበር፤ “… በማለዳ ጊዜ ነጐድጓድና መብረቅ ከባድም ደመና እጅግም የበረታ የቀንደ መለከት ድምጽ በተራራው ላይ ሆነ፤ በሰፈሩም የነበሩት ሕዝብ ሁሉ ተንቀጠቀጡ።” (ዘጸ. 19፥16) እንዲል፣ እግዚአብሔር ለእስራኤል ልጆች ሲገለጥ፣ ማንም ሊቀርበው በማይችል መንገድ ነው፤ እንኳንና እግዚአብሔርን ርሱ የሚገለጥበትን ተራራ መንካት የማይታሰብ ነገር ነው፤ “… ወደ ተራራው እንዳትወጡ ጫፉንም እንዳትነኩ ተጠንቀቁ፤ ተራራውንም የነካ ፈጽሞ ይሞታል፤” (ዘጸ. 19፥12)። እጅግ በሚያደንቅና በሚገርም መንገድ የፊተኛው ኪዳን ሊቀ ነቢያት ሙሴ እንኳ፣ “በፍርሃት ተንቀጠቀጥሁ” ብሎአል፤ (ዕብ. 12፥21)።

Saturday, 27 December 2025

ወንድሞችን ለምን አምናቸዋለኹ?

 Please read in PDF

በአዲስ ኪዳን ወይም በመላው ክርስትና ውስጥ፣ እግዚአብሔር በብዙ ጸጋውን ያበዛለትና በወንጌል አገልግሎት ብዙ ሺህ ማይሎችን ተጉዞ በማገልገል እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ምሕረት የገነነለትና የተትረፈረፈለት ብርቱ አገልጋይ “ያለ አይመስልም”። የጽድቅ ቀናተኛ፣ የማያመቻምች፣ ባለ ብዙ ሐብተ ጸጋ፣ አያሌ አብያተ ክርስቲያናትን የመሠረተ፣ የአዲስ ኪዳንን ግማሽ ያህል መጻሕፍት የጻፈ፣ አስደናቂና ተወዳጅ የእግዚአብሔር ምስጢራትን በትምህርትና በስብከት የመገበ፣ ክርስቶስን አክብሮና አስከብሮ በሕይወቱ ጭምር መስክሮ በጽድቅ መሥዋዕት የኾነ ሐዋርያ ነው።

Friday, 5 December 2025

የታይታ አገልግሎት የለንም!

Please read in PDF

ሽልማታችን ሰማይ፤ ዋጋችን ኹሉን በዓይኑ በሚቆጣጠር ጌታ ዘንድ እንደ ኾነ አውቀንና አምነን፣ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው የተከተሉ የጽድቅ መናንያን፤ የቅዱስ ቃሉን ሰማዕታት፤ እንደ ጨው በምድር ዳርቻዎች ኹሉ የተበተኑ ሐዋርያትን፤ እውነትና ፍትሕን እንደ ውኃ ከፈሰሰ ሕይወት ጋር የሰጡ ነቢያትን፤ ታርዶ እንደ ተወራረደ መሥዋዕት ኹለንተናቸውን የሰጡ ሰባክያንን፤ የምድረ በዳውን ዋዕይ፣ የበረሃውን ሚራዥ ታግሠው ሳይናወጡ የተጉና የኖሩትን እንደ ደመና ዙሪያችን ዘወትር የከበቡንን “ሕያዋን ጻድቃንን” አሠረ ፍኖታቸውን የምንከተል የተሰቀለው መሲሕ ማኅበረ ሰብ ነን። እናም መሲሑ እንዲልቅ፤ መንግሥቱ እንዲሰፋ፤ ለቤተክርስቲያን ጥቅምና መታነጽ እንጂ ለታይታ የምናደርገው አንዳችም የለንም።

Wednesday, 3 December 2025

ከዶክተር ገመቺስ ምክር ተጠበቁ!

 Please read in PDF

ከሰሞኑ ዶክተር ገመቺስ እንዲህ ብሎአል፤

ዳዊት ድሪምስ የወደቀውን የሰውን ሥነ ልቦና ለማነሳሳት የሚተጋ ሰው እንጂ የአዲሱ ዘመን ዕሳቤ አራማጅ አይደለም።”

ስለ አዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አማኞችና ተከታዮች በሰፊውና በተከታታይ መጻፋችን ይታወሳል። ዶ/ር ገመቺስ ፈጽሞ እንደ ተናገረው ሳይኾን፣ እነ ዳዊት ድሪምስ፣ አሸናፊ ታዬ፣ ኤልያስ ገብሩ(ዶ/ር)፣ ግማዊት ክፍሌ፣ ነፃነት ዘነበ፣ ማንያዘዋል እሸቱና ሌሎችም በአገራችን የትምህርቱና የልምምዱ ዋና አቀንቃኞች መኾናቸውን አንስተን ጽፈናል፤ ዛሬ ደግሞ ዶክተሩ፣ ስለ ዳዊት ድሪምስ የተናገረውን በጥቂቱ እንቃኝ።

Friday, 21 November 2025

የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ (የመጨረሻው ክፍል)

 Please read in PDF

የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ፦

6.    በልምምዱ ጥንቁልናና አስማትን ያበረታታል፦ ኮከብ ቈጠራ እና ጥንቈላ፡ ለራስ ለውጥ እና ማስተዋል የሚያገለግሉ ሟርት አክል መሣሪያዎችን በጽኑ ይደግፋሉ። በራሳቸው ይህን ቢደግፉና ቢቀበሉ ማንም አይቃወማቸውም፣ ምክንያቱም “የትኛውም ሰው የፈለገውን ሃይማኖት የመከተል መብቱ የተጠበቀ ነው። ነገር ግን የሮንዳ በርንን፣ የቦብ ፕሮክተርን፣ የድፓክ ቾፕራንና የኤካርት ቶልን፣ የማሪያን ዊልያምሰን፣ የባርባራ ማርክስ ሁባርድ፣ የኒሌ ዶናልድ ዋልሽ፣ የባርባራ ዴአንጀሊስ፣ የላቫር በርተን፣ የሪቻርድ ካርልሰን፣ የቤቲ ኢዲ፣ የኬን ፎሌት ወይም ደግሞ የእንቅስቃሴው አባቶች የሚባሉትን የአሊስ ቤይሊ፣ የቴይልሃርድ ዴ ቻርዲን፣ የሮበርት ሙለር፣ የዴቪድ ስፓንገር እና የቤንጃሚን ክሬም የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አስተምህሮን እያቀነቀኑ የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ነኝ ማለት ፈፅሞ አይቻልም።”


Wednesday, 12 November 2025

የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፯

 Please read in PDF

4.    እውነት አንጻራዊ ናት፦ በአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አስተምህሮ መሠረት ፍጹም እውነት የለም፤ ምክንያቱም ኹሉም እምነቶች ትክክልና ትክክለኛ ናቸው። ለምሳሌ፦ በክርስትና አስተምኅሮ አንድ ሰው ከጋብቻ ውጭ የሚያደርገው ማናቸውም ሥነ ምግባራዊ ርኩሰት አመንዝራነት ነው፤ ለአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ግን ርኩሰት ሳይኾን ትክክል ነው። በጋብቻ ውስጥም፤ ከጋብቻ ውጭም የሚደረግ አመንዝራት እውነትና ውሸት ቢኾንም፣ ለነርሱ ግን ኹለቱም እውነት ነው።

Friday, 7 November 2025

ቤን ሂንና ኑፋቄው!

 Please read in PDF

ሰውየው አስቀድሞ መጠሪያው “Faith World Church - የእምነት ዓለም ቤተክርስቲያን” በተባለ፣ በአኹን ወቅት ደግሞ World Healing Center Church - የዓለም የፈውስ ማዕከል ቤተክርስቲያን” የሚል ስያሜ የተሰጠው የግል “ቤተ ክርስቲያን” ያለውና “የብልጽግና ወንጌልን” አቀንቃኝ “ንጥጥ ባለጠጋ” ነው። ከባለጠግነቱና ከቅምጥልነቱ የተነሣ፣ የሂን የወንድም ልጅ የኾነው ፓስተር ኮስቲ ሂን በርሱ ቤት ተጠልሎ ሳለ ያየውን ሲናገር፣ ቅዱስ ጳውሎስና እነርሱ የሚለያዩበትን አንድ እውነት፣ “እኛ የጳውሎስን አይነት ወንጌል አንሰብክም ነበር።” በማለት ገልጦታል።[1] በምስክርነቱ ላይ ኮስቲ ሂን፣ እሱ እና ቤተሰቡ የያዙትን ውድ መኪናዎች እና ውድ ቤቶችን እና በጉዞው ዙሪያ ስላለው የቅንጦት ኹኔታ ገልጦአል።[2] ኮስቲ ሂን የአጎቱን የብልጽግና ወንጌል እና አስተምህሮ በመተቸት ብዙዎቹ ትንቢቶቹ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር እንደሚቃረኑ ጽፎአል።[3]

Tuesday, 4 November 2025

ቃሉን የሚያነብብ ብፁዕ ነው!

 Please read in PDF

ቅዱስ ቃሉን ማንበብ መንፈሳዊና ታላቅ አምልኮ ነው፤ አቡቀለምሲሱ ቅዱስ ዮሐንስ፣ “[ቅዱስ ቃሉን] የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።” (ራእ. 1፥3) ይለናል። ሐዳሲው ቅዱስ ዕዝራ፣ “... ወንዶችና ሴቶች የሚያስተውሉም ሲሰሙ፥ ከማለዳ ጀምሮ እስከ ቀትር ድረስ አነበበው የሕዝቡም ሁሉ ጆሮ የሕጉን መጽሐፍ ለመስማት ያደምጥ ነበር።” (ነህ. 8፥3) እንዲል፣ ቃሉን ከእኩለ ቀን በላይ ማንበብ እጅግ ታላቅ አምልኮ ነው።

Friday, 24 October 2025

የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፮

 Please read in PDF

3.    ክርስቶስ የመዳን ራስ እንደ ኾነ የሚታመነውን የክርስትና ዋና እምነት ጨርሰው ይክዳሉ፦ በአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አስተምኅሮ መሠረት፣ ኢየሱስ ክርስቶስ አንድ “ዮጊ” ወይም “የዕውቀት ብርሃን ያገኘ የበራለት ሰው ብቻ” ነው። ይህም ብቻ ሳይኾን፣ ርሱን ፍጹም አምላክ ነው ብሎ ማመንና ማምለክ፣ መጥፎና ሰዎችን ‘እውነተኛ ኃይላቸውን’ ከማወቅ ለማራቅ የታለመ የውሸት ትምህርት ነው ብለው ያምናሉ፤ ያስተምራሉም።

Thursday, 16 October 2025

የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፭

 Please read in PDF

በባለፈው ክፍል እንደ ተመለከትነው፣ የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አስተማሪዎች፣ የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣንን ጨርሶ እንደማይቀበሉና እንደሚያቃልሉ አንስተናል፤ በዚሁ ዐሳብ ላይ ጥቂት እንጨምርና ወደሚቀጥለው እንሄዳለን።

የጽድቅ መንፈስ የኾነው መንፈስ ቅዱስ ወደ ጽድቅና ቅድስና የሚመራና ደግሞም እርሱ የቅዱስ ቃሉ ባለቤትና ደራሲ ነው፤ ስለዚህም ቅዱስ ቃሉ የሕይወታችን፣ የአምልኮአችን፣ የአገልግሎታችን፣ የአስተምኅሮና የምልልሳችን ኹሉ ማዕከልና ቃኚ ነው። ቃሉን በመንፈስ ቅዱስ አብርሆት በትክክል ሳንረዳ ተሳስተን ብንወድቅ፣ እኛ እንጎዳለን እንጂ ቃሉ እውነተኛና የታመነ ነው። “ባናምነው፥ እርሱ የታመነ ሆኖ ይኖራል፤ ራሱን ሊክድ አይችልምና።” እንዲል (2ጢሞ. 2፥13)።

Sunday, 12 October 2025

የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፬

 Please read in PDF

አስቀድመን እንደ ተናገርነው፣ “ኒው ኤጅ ሙቭመንት”[1] አዲስ “እምነት” እንደሚመስል ስያሜው ቢናገርም፣ ነገር ግን ትምህርቱ፣ ከኖስቲዝም፣ ከክርስትና ከሂንዱና ከሌሎችም ቤተ እምነቶች የተቀዳና የተለቃቀመ ትምህርት ነው።[2] ከክርስትና በቀዳው አመለካከቱ ስለ እምነት የሚናገር ቢመስልም፣ ዕውቀትን በማምለክ ደግሞ ኖስቲዝምን “ቁርጥ ነው”፤ በልምምዶቹ ከጥንቁልና ጋር ቢመሳሰልም፣ ክርስቲያኖችን ለመምሰል ግን ከመጽሐፍ ቅዱስ በመጥቀስ ደግሞ “የሰይጣንን ብርሃናዊ መልክ” ለመያዝ ይጥራል!

Saturday, 27 September 2025

የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፫

 Please read in PDF

በባለፉት ክፍሎች ግቦቻቸውንና ዋና ዋና አስተምኅሮአቸውን ማየታችንን እያስታወስን ዛሬም ቀጣዩን ዋና ዋና አስተምኅሮአቸውን እናነሳለን። የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አማኞች፦

3.   ክርስቶስ አንድ “ዮጊ” ነው፤ ነገር ግን ከርሱም የሚበልጡና የላቀ መገለጥ ያላቸው “ዮጊዎች” እንዳሉ ያምናሉ። ኢየሱስ ብሩህ አስተማሪ ነበር፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ልጅ አልነበረም በማለት ያስተማራሉ። ከዚሁ ጋ በተያያዘ የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አማኙና አስተማሪው ኤልያስ ገብሩ(ዶ/ር) የተባለ ሰው፣ ራሱን ከእግዚአብሔር ለማስተካከልና ኹሉም ነገር በውስጡ እንዳለ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች “ቦጫጭቆ በመስፋት” እንዲህ ይላል፣

Friday, 26 September 2025

መስቃላና መስቀል ምን አገናኛቸው?

 Please read in PDF

ዋቄፈታ ዋቃ ከሰማይ አውርዶልናል ብሎ ከሚያምናቸው አያሌ በአላት መካከል አንዱ የመስቀላ በአል ነው፤ ካልታተመው መጽሐፌ ዋቄፈታ ስለ መስቀላ የሚያምነውን እንዲህ አስነብባችኋለሁ፤

“ … በአሉ በሌሎች ስፍራዎች፣ “ዳሞቲ” እየተባለ ይጠራል።[1] “ሁሉቆ” ብለውም የሚጠሩት አሉ፤[2] ችግሮችንና ክፉውን መናፍስት ለማራቅ የጉባ ወይም የማቃጠል ሥርዓት ይከናወናል።[3] ይህ በአል “ጉባ” ተብሎ በሰሜን ሸዋ አከባቢ ነሐሴ 16 ቀን ይከበራል። በአብዛኛው ቦታ ደግሞ ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የ“መስቀል” ክብረ በአል ጋር ተያይዞ የሚከበር ነው።