Sunday, 18 January 2026

ተጠመቀ ጌታ!

 Please read in PDF

ርደተ ገሃነም ርደተ መቃብር

በመርገመ ሥጋም የነፍስ ሲጨመር

ጽሕፈተ ዕዳችንም ደልቦ ወርዝቶ

Tuesday, 6 January 2026

አስፈሪው አምላክ በትህትና ንጉሥነቱ

 Please read in PDF

በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ለኪዳኑ ሕዝብ የተገለጠበት መንገድ እጅግ አስደናቂም፤ አስፈሪም ነበር፤ “… በማለዳ ጊዜ ነጐድጓድና መብረቅ ከባድም ደመና እጅግም የበረታ የቀንደ መለከት ድምጽ በተራራው ላይ ሆነ፤ በሰፈሩም የነበሩት ሕዝብ ሁሉ ተንቀጠቀጡ።” (ዘጸ. 19፥16) እንዲል፣ እግዚአብሔር ለእስራኤል ልጆች ሲገለጥ፣ ማንም ሊቀርበው በማይችል መንገድ ነው፤ እንኳንና እግዚአብሔርን ርሱ የሚገለጥበትን ተራራ መንካት የማይታሰብ ነገር ነው፤ “… ወደ ተራራው እንዳትወጡ ጫፉንም እንዳትነኩ ተጠንቀቁ፤ ተራራውንም የነካ ፈጽሞ ይሞታል፤” (ዘጸ. 19፥12)። እጅግ በሚያደንቅና በሚገርም መንገድ የፊተኛው ኪዳን ሊቀ ነቢያት ሙሴ እንኳ፣ “በፍርሃት ተንቀጠቀጥሁ” ብሎአል፤ (ዕብ. 12፥21)።