ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ከክርስቶስ ትምህርት፣ ሕይወትና ሥራ አንጻር ተሐድሶ እንደሚያሻት ለጥያቄ የማይቀርብ ሐቅ ነው። በተደጋጋሚ ቤተ ክርስቲያኒቱ ራስዋ፣
“ተሐድሶ እንደሚያሻት” ስትናገር ሰምተናታል። ከዚኹ ጋር በተያያዘ፣ “ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማደስ” ከሚንቀሳቀሱ አካላት ሦስት ዓይነት
ተግዳሮቶች በግልጥ ይታያሉ፤
Sunday, 31 August 2025
“ተሐድሶ ነን” ባይ የተሐድሶ ተግዳሮቶች!
Wednesday, 27 August 2025
“ሄደህ …ስበክ”! (ዮና. 1፥1)
እግዚአብሔር አምላክ የተልእኮ አምላክ ነው። አስቀድሞ ሰው በኀጢአቱ በወደቀ ጊዜ ለማንሳት ወደ ወደቀበት ስፍራ፣ “ወዴት ነህ?” (ዘፍ. 3፥10) እያለ ፍለጋ የመጣው ያህዌ ኤሎሂም ነው። እግዚአብሔር ፍጥረት በወደቀ ጊዜ በመፈለጉና ፈልጎም በማግኘቱ፣ የተልእኮ አምላክ ነው። ርሱ ፍጥረት በመውደቁ ደስ አይሰኝም፤ “የምዋቹን ሞት አልፈቅድምና፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ስለዚህ ተመለሱና በሕይወት ኑሩ።” (ሕዝ. 18፥32) እንዲል።
Thursday, 14 August 2025
የ“እውነት ቃል አገልግሎት” እና ሕግ!
የ“ሥፍረ ዘመን አማንያን” ትምህርቶቻቸው ከተመሠረቱባቸው መሠረታዊ ትምህርቶች አንዱ፣ የሕግና የጸጋ አስተምኅሮአቸው ነው። ጸጋን እጅግ ከመለጠጣቸውም የተነሳ፣ ስለ ሕግ አንዳችም ነገር እንዲነገር አይፈልጉም፤ ከዚህ ስሑት አስተምኅሮአቸው ነጻ የወጣው ሚስተር ማውሮ ሲናገር እንዲህ ይላል፣ “ … በእግዚአብሔር ቅዱስ ሕግ ላይ የሚጥሉት ምኞቶች በጠቅላላው ሙሉ እና ከባድ ደግሞም የተሳሳተ መግለጫ ነው።”
Sunday, 3 August 2025
የትዝታው ሳሙኤል ኮንሰርት ምን ገለጠልኝ?
ይህን ጽሑፍ ለመጻፍ ብዙ አመንትቻለኹ፤ ለተሐድሶ አገልግሎት ከማይመቹ አካሄዶች መካከል የነትዝታውን የሚመስል አስከፊ መንገድ የለም፤ እነ ትዝታው ከ“አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል” ውስጥ ራሳቸውን አዳብለዋል፤ ይኹንና ካውንስሉ በውስጡ፣ የክርስቶስን ርቱዕ ትምህርት፣ ሕይወትና ሥራ የማይቀበሉ ያሉትን ያህል፣ እነ ትዝታውም እውነተኛ የወንጌላውያን አማኞች እንዳልኾኑ የሚያሳዩ አያሌ ምልክቶች አሉ።