Sunday, 31 August 2025

“ተሐድሶ ነን” ባይ የተሐድሶ ተግዳሮቶች!

Please read in PDF

ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከክርስቶስ ትምህርት፣ ሕይወትና ሥራ አንጻር ተሐድሶ እንደሚያሻት ለጥያቄ የማይቀርብ ሐቅ ነው። በተደጋጋሚ ቤተ ክርስቲያኒቱ ራስዋ፣ “ተሐድሶ እንደሚያሻት” ስትናገር ሰምተናታል። ከዚኹ ጋር በተያያዘ፣ “ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማደስ” ከሚንቀሳቀሱ አካላት ሦስት ዓይነት ተግዳሮቶች በግልጥ ይታያሉ፤

Wednesday, 27 August 2025

“ሄደህ …ስበክ”! (ዮና. 1፥1)

 Please read in PDF

እግዚአብሔር አምላክ የተልእኮ አምላክ ነው። አስቀድሞ ሰው በኀጢአቱ በወደቀ ጊዜ ለማንሳት ወደ ወደቀበት ስፍራ፣ “ወዴት ነህ?” (ዘፍ. 3፥10) እያለ ፍለጋ የመጣው ያህዌ ኤሎሂም ነው። እግዚአብሔር ፍጥረት በወደቀ ጊዜ በመፈለጉና ፈልጎም በማግኘቱ፣ የተልእኮ አምላክ ነው። ርሱ ፍጥረት በመውደቁ ደስ አይሰኝም፤ “የምዋቹን ሞት አልፈቅድምና፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ስለዚህ ተመለሱና በሕይወት ኑሩ።” (ሕዝ. 18፥32) እንዲል።

Thursday, 14 August 2025

የ“እውነት ቃል አገልግሎት” እና ሕግ!

 Please read in PDF

የ“ሥፍረ ዘመን አማንያን” ትምህርቶቻቸው ከተመሠረቱባቸው  መሠረታዊ ትምህርቶች አንዱ፣ የሕግና የጸጋ አስተምኅሮአቸው ነው። ጸጋን እጅግ ከመለጠጣቸውም የተነሳ፣ ስለ ሕግ አንዳችም ነገር እንዲነገር አይፈልጉም፤ ከዚህ ስሑት አስተምኅሮአቸው ነጻ የወጣው ሚስተር ማውሮ ሲናገር እንዲህ ይላል፣ “ … በእግዚአብሔር ቅዱስ ሕግ ላይ የሚጥሉት ምኞቶች በጠቅላላው ሙሉ እና ከባድ ደግሞም የተሳሳተ መግለጫ ነው።”

Sunday, 3 August 2025

የትዝታው ሳሙኤል ኮንሰርት ምን ገለጠልኝ?

 Please read in PDF

ይህን ጽሑፍ ለመጻፍ ብዙ አመንትቻለኹ፤ ለተሐድሶ አገልግሎት ከማይመቹ አካሄዶች መካከል የነትዝታውን የሚመስል አስከፊ መንገድ የለም፤ እነ ትዝታው ከ“አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል” ውስጥ ራሳቸውን አዳብለዋል፤ ይኹንና ካውንስሉ በውስጡ፣ የክርስቶስን ርቱዕ ትምህርት፣ ሕይወትና ሥራ የማይቀበሉ ያሉትን ያህል፣ እነ ትዝታውም እውነተኛ የወንጌላውያን አማኞች እንዳልኾኑ የሚያሳዩ አያሌ ምልክቶች አሉ።