Please read in PDF
የኢየሱስ ደም አገልግሎት
“ከኃጢአት ሁሉ የሚያነጻ” (1ዮሐ. 1፥9)
“በእግዚአብሔር ፊት ስለ እኛ አሁን የሚታይ” (ዕብ. 9፥24)
“በቅዱስ ደሙ ኃጢአታችንን የሻረ” (ትምህርተ ኅቡዐት)
የኢየሱስ ደም አገልግሎት
“ከኃጢአት ሁሉ የሚያነጻ” (1ዮሐ. 1፥9)
“በእግዚአብሔር ፊት ስለ እኛ አሁን የሚታይ” (ዕብ. 9፥24)
“በቅዱስ ደሙ ኃጢአታችንን የሻረ” (ትምህርተ ኅቡዐት)
ቅዱስ እግዚአብሔር በበጎ ፈቃዱና ከታላቅ ባዕለጠግነቱ የተነሳ ሰውን ፍጹምና ቅዱስ አድርጎ ከመፍጠሩ በፊት የተፈጠረው ክቡር ፍጡር በገዛ ፈቃዱ ወድቆ እንደሚረክስ በባሕርይ ዕውቀቱ አወቀ። ስለዚህም የሚፈጥረውን ውድ ፍጥረት አብ በልብ እንዳሰበ በወልድ ሕያው ቃልነት ሲፈጥረው፤ መጥቶ እንደሚያድነውና እንደሚዋጀው ኪዳንን ገባ። ይስሐቅ በአብርሐም ኅሊና ቀድሞ እንደታረደ ወልድም በአብ ኅሊና ቀድሞ የታረደ ሆኖ በበጉ ያመኑትና የዳኑት ቀድሞ ስሞቻቸው በሕይወት መዝገብ ተጻፈ፤መንፈስ ቅዱስ ይህን እውነት ቀድሞ ለተወሰኑ ምርጦች በብሉይ ኪዳን ኋላም ለሐዲስ ኪዳን አማኞች ናኘው።