Sunday, 23 September 2018

ይድረስ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ዓቢይና ለክቡር የኦሮሚያ ክልል ፕረዘዳንት ለማ መገርሳ!

Please read in PDF

   አስቀድሜ ትልቁን የሰማይ አምላክ አንተ ብዬ በምጠራበት ዓውድ፣ ከኹለት አንዳችሁን ሳነሣ “አንተ” ብዬ ብጣራ “ባህል ጣሽ፣ አክብሮት ገሳሽ” [በምን አቅሜ - አንድዬ እያለ] አንባቢዎቼም እናንተም እንደማትሉኝ በመተማመን ነው። ስለዚህም አንተ ብዬ በምናገርበት ቦታ ላይ የንቀት ወይም ሌላ ምንም ነገር በውስጤ እንደ ሌለ አስቀድሜ መናገር እፈልጋለሁ።
    መቼም፣ “ይህ ጽሑፍ በየት በኩል ለእነርሱ ይደርሳል?” እንዳልባል፣ ኹለቱም መገናኛ ብዙሃንንና ማኅበራዊ መገናኛዎችንም በቅርብ ተከታታይ መኾናቸውን በተለያየ መንገድ አጣርቻለሁ፤ ከዚህ ባሻገር ኹለቱም በጽሕፈት ቤታቸው ብዙዎች የሚከታተሉት ማኅበራዊ መገናኛዎች አሏቸው፤ እናም ሊደርሳቸው እንደሚችል በማሰብ በእርግጠኝነት መጻፍን መርጫለኹ። ልጽፍ ያነሳሳኝ ዓቢይ ነገር ልቤ ላይ ደጋግሞ ስለመጣና ውጤቱንም በተደጋጋሚ በማየቴ፣ በሌሎች አገራትም ላይ ተመሳሳይ የታሪክ ስህተት መፈጸሙን በማስተዋሌም ጭምር ነው። የዚህ ጽሁፍ ዋነኛ ዓላማ፣ ኀጢአትን ለመኰነን ብቻ እንጂ የማንንም ባህልና ወግ የሚነካ ተግባርን የሚያካትት አይደለም።

Wednesday, 19 September 2018

“ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች” (መዝ. 42)

  የዳዊት መዝሙሮች፣ የብዙ ቅዱሳን ሰዎች ስብስብ መዝሙር ነው። ከእነዚህ አንዱ ደግሞ መዝ. 42ን በምሳሌነት መጥቀስ እንችላለን። መዝ. 42 ጠቅላላው በስደት ላይ ያለ አንድ ሌዋዊ የሚያለቅሰውን ልቅሶ የሚመለከት ነው። ከልቅሶው ውስጥ “ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ፥ አቤቱ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች፤ መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ? ዘወትር፦ አምላክህ ወዴት ነው? ሲሉኝ እንባዬ በቀንና በሌሊት ምግብ ኾነኝ።” (ቁ. 1-3) የሚለው ክፍል እጅጉን ልብ የሚሰብር ክፍል ነው።

   መዝሙሩን የዘመረው ሌዋዊ ከቆሬ ወገን የኾነ፣ የቤተ መቅደስ አገልጋይና በቤተ መቅደሱ በታማኝነት እግዚአብሔርን የሚቀድስ፣ የሚወድስ፣ የሚባርክ የነበረ ነው። ሌዋዊው የመሰደዱና ከአገሩ የመነቀሉ ምክንያት የእርሱ ኀጢአት ይኹን የሕዝቡ ኀጢአት በግልጥ አልተገለጠም፤ ከምንም በላይ ግን ጠንካራ የኾነ የእንባ ዘለላና ስብራት ከብቦታል። ሌዋዊው በልቅሶው ውስጥ በጠንካራ ሃዘን ተከብቧል፤ ከፍ ባለው ሃዘኑ ውስጥ ደግሞ በቤተ መቅደሱ ውስጥ በእግዚአብሔር ፊት ለመኾን ያለውንም ጉጉት ያመለክታል። ይህን ታላቅ መሻትና ጉጉቱን ግን ኀጢአት ወይም የአስጨናቂዎቹ እገታ ገድቦታል።

Sunday, 16 September 2018

ማኅበራዊ ድረ ገጾችን ለወንጌል አገልግሎት የመጠቀም አዎንታዊና አሉታዊ ተጽዕኖዎች

  “ዘመናችን ከሸማኔ መወርወርያ ይልቅ በሚቸኩልበት” (ኢዮብ 7፥6) በዚህ ወራት ነገሮች፣ ክስተቶች፣ ሁኔታዎች … ካሰብነው በተቃራኒው ወይም ካሰብነው በላይ ወደሆነ ጫፍ መፍሰሳቸው አይቀሬ ጉዳይ ነው። ለዚህ ደግሞ “አለምን ወደ አንድ መንደርነት እያመጧት” ያሉት የማኅበራዊ ድረ ገጻት ማለትም የኢንተርኔት፣ የሞባይል፣ የሳተላይት ቴሌቪዥን ግንኙነቶችና ሌሎችም ማኅበራዊ ድረ ገጻት በጎም ይሁን አሉታዊ ተጽዕኖዎች መኖሩ ክርክር የሚነሳበት ጉዳይ አይደለም።
    ቤተ ክርስቲያን “ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው” (ማቴ. 28፥19) የሚለውን ሐዋርያዊ ታላቁ ተልእኮዋን መጠበቅና መፈጸም የሚቻላት፣ የሚድኑ ነፍሳትን የምታገኝባቸውን እድሎች አሟጣ ስትጠቀም ነው። ለምሳሌ፦ ፌስ ቡክ ወደ አንድ ነጥብ ሦስት ቢሊየን ገደማ አባላት ያሉት ሲሆን፣ ይህንን እውነታ ወደ እውነተኛው ዓለም ብናመጣው በ2016 ቆጠራ የተደረገለትን 1.2 ቢሊየን ገደማ የሚጠጋውን የአፍሪካን ሕዝብ ሽፋን ያካልላል ማለት ነው። ይህም የአድማሱን ሽፋን ብቻ ሳይሆን፣ በውስጡ የሚያስተላልፈው መልዕክት በቀጥታ ይሁን በተዘዋዋሪ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት “መደገፉ” አልያ ፍጹም መቃረኑ አይቀሬ ነው።

Sunday, 9 September 2018

ዘመን - የእግዚአብሔር የቸርነት ስጦታ


 ስለበላን ወይም ስለጠጣን፣ ለብሰን ስላማረብን ወይም እናት አባት፣ ጉልበት ስላለን ወይም መውጣት መግባት ስለቻልን፣ የአገራችን መሪዎች ደግ ወይም ክፉ ስለ ኾኑ፣ ደመወዛችን ስለ ተደላደለ ወይም የንግድ ወረታችን ስላማረበት ወይም ስለ ተትረፈረፈ ከዚህ አልደረስንም፤ ደግሞም ይህ የኾነልን በአጋጣሚ ወይም ከሌሎች የተሻለ ጽድቅና መልካምነት ስላለን፣ እንዲሁ ደግሞ ሌሎች ክፉዎችና እጅግ አላስፈላጊዎች ስለ ነበሩ ተወግደው ለእኛ ዘመን የተጨመረልን፣ ዕድሜ የተሰጠን አይደለም። አዎን! በሕይወታችን ዕድል፣ ዕጣ ፈንታ፣ አጋጣሚ፣ ድንገት፣ የአርባና የሰማንያ ቀን ጽዋ የሚባል ነገር ተሳክቶልን ከዚህ አልደረስንም።

Tuesday, 4 September 2018

የአዲስ ዓመት ስጦታ!

በቅርቡ በክርስትና "ዕቅበተ እምነት" ላይ የሠራኹትና የማስነብበው የመጀመሪያ መጽሐፌ፤ ምናልባትም ለብዙዎች የአዲስ ዓመት ክቡር ስጦታዬ! ጌታዬ ኢየሱስ ይህን ሥራ ስሠራ በብዙ ረድቶኛል! ክብር ለእርሱ ይኹን፤ አሜን።

                                           

የእኛው ቤት ጸበልና የአ.ተ.ት ወረርሽኝ


Please read in PDF

ከጵንኤል ያዕቆብ(Peniel Jacob) የፊት ገጽ (facebook) የተወሰደ



"ጸበል" ለአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አ.ተ.ት) ወረሽኝ መዛመት፥ ምክንያት ከሆኑት መካከል ዋነኛው መኾኑን የተለያዩ የጤናና የመንግስት ተቋማት በማሳሰብ ላይ ናቸው፡፡ የአ.ተ.ት ወረሽኝ ከሰውነታችን ውስጥ ያሉ ጠቃሚ ፈሳሻችን በተቅማጥ እና በትውከት መልኩ በመውጣት የሰው ልጅን ለህልፈት የሚዳርግ በሽታ ነው፡፡ (የጤና ባለሙያዋ ውዷ ባለቤቴም፥ እንደነገረችኝም ከኾነ አ.ተ.ት ይባል እንጂ የኮሌራ ወረሽኝ መኾኑን ነው)፡፡ ይሄም እንግዲህ፤ ሌላኛው የእኛው ቤት ዕዳ ነው፡፡ ለማስረጃነት ይረዳን ዘንድ፥ ከዚህ በታች የሰበሰብኳቸውን የተለያዩ ተቋማት ሪፖርት እንመልከት፥

Thursday, 30 August 2018

ቤተ ክርስቲያንም ከደቦ ገዳዮች እንደ አንዱ ስትኾን!

   Please read in PDF

ቤተ ክርስቲያን እንኳን የተፈጸመን ያልተፈጸመን ኀጢአት ማየት የምትችልበትን ነቢያዊ ችሎታ በመንፈስ ቅዱስ ተችሯታል። ኀጢአትን ለመቃወምና ለመጠየፍ፤ አለማዊነትንም ለመካድ ጭምር በክርስቶስ ኢየሱስ የተገለጠ የእግዚአብሔር ጸጋ ለቤተ ክርስቲያን ተገልጧል፤ (ቲቶ 2፥11-13)። ቤተ ክርስቲያን ይህን የተገለጠ ጸጋ በእውነት በመቀበልና በማመንም ጭምር፣ የሰማይ መንግሥት እንደ ራሴነቷን ማስቀጠል ይኖርባታል። ቤተ ክርስቲያን ይህን ዘላለማዊ አደራ ይዛ ለመሄድ ግን የሞተላትንና አንድ ቤዛዋን ክርስቶስ ኢየሱስን ትኵር ብላ መመልከት የዘወትር ተግባርዋ ሊኾን ይገባል።
  ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታችንን እንደ ተሰቀለ ኾኖ ትኵር ብሎ አለማየት ለድንዛዜና ለክፋት፤ ለእውነት ለማያሳዝዝ አዚም ሳያጋልጥ አይቀርም፤ (ገላ. 3፥1)፤ አዚም የአእምሮ ችግር አይደለም፤ ራስንም የመሳት ጉዳይ አይደለም፤ ፍጹም አለማወቅና አለመረዳትም አይደለም፤ ነገር ግን መረዳት እየቻሉ አለመረዳት፣ ማስተዋል እየቻሉ ተላላ በመኾን አለማስተዋል፣ ማየት እየቻሉ መታወር፣ መጠንቀቅ እየቻሉ ፍጹም ቸለተኛ የመኾን ጉዳይ ነው። የገላትያ ቤተ ክርስቲያን ፊት ለፊቷ ያለውን እውነት በዝንጉነትና በቸለተኝነት ባለማስተዋል በአዚም ተያዘች። እናም የተሰቀለውን ክርስቶስን ባለማየት ስንፍና ተያዘች።

Thursday, 23 August 2018

የሊቀ ጳጳሳት ፍራንሲስ ማሳሰቢያ ኹላችንን አይመለከትምን?

    የካቶሊኩ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፍራንሲስ፣ “ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን በቀሳውስቷ በልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወሲባዊ ጥቃት የመከላከል እንዲህ ያለ አድራጐት ተፈጽሞ ቢገኝ እንኳ አንዳትሸፋፍን የሚያደርግ ባህል ለማረጋገጥ አስፈላጊው ጥረት ሁሉ መደረግ እንዳለበት” ዛሬ ከጽሕፈት ቤታቸው አስታውቀዋል። ይህ እጅግ አስደናቂም አሰቃቂም ውሳኔ ነው፤ ይህን ስሰማ ቤተ ክርስቲያን እንዴት ባለ ነውር ተጠልፋ መውደቋን ደጋግሜ አሰብሁ፤ ውስጤም በጽዩፍ መንፈስ ኾኖ ተቈጣ።


Wednesday, 22 August 2018

ከሆነኝ ኢየሱስ!

Please read in PDF

ጠዋት በማለዳ ሲመሽም በሠርኩ
በኃጢአት ወድቄ ድኼ እያለቀስኩ
መሐሪ ፍለጋ ለበደሌ ይቅርታ

Wednesday, 15 August 2018

በሥጋ የተገለጠ አምላክ


    የክርስትና ትምህርት የመገለጥ ትምህርት ነው። የመገለጡ ምንጭ መለኮት ከኾነው ከራሱ ከእግዚአብሔር እንጂ፣ በሰው ወይም ከሰው አይደለም። ይህ መገለጥም “ከጥንት ጀምሮ በብሉይ ኪዳን ታሪክ እግዚብሔር በልዩ በልዩ መንገድ ለአበውና ለነቢያት በቃልም ሆነ በድርጊት፣ በራእይም ሆነ በሕልም በተአምራዊ ሁኔታ የገለጠላቸውን ሁሉ ያካትታል፤ በተለይም በኋለኛው ዘመን በሥጋ የተገለጠውን ክርስቶስንና የማዳን ሥራውን ሁሉ ይመለከታል።”[i]

ከዋናው መገለጥ በፊት የነበረው “መገለጥ”
     ብሉይ ኪዳን ታላቁን መገለጥ ፍለጋ ብዙ የመቃተት ድምጾች፣ ሕልሞች፣ ራእዮች፣ ትንቢቶች … የተሰማበት የምጥ መጽሐፍ ነው። እኒህ ብዙ መቃተቶችና ፍለጋዎች ለረጅም ዓመታት የተደረጉ ናቸው። በእኒህ ረጅም ዘመናት መላእክት ሊያዩት የሚመኙትንና ሰዎች ሊያገኙት ያላቸውን መዳን፣ ቅዱሳን ነቢያት “…ተግተው እየፈለጉ መረመሩት፤” (1ጴጥ. 1፥10-11)፣ ታላቁ ነቢይ ሙሴ፦ “የእግዚአብሔር ሕዝብ ሁሉ ነቢያት ቢሆኑ፥ እግዚአብሔርም በእነርሱ ላይ መንፈሱን ቢያወርድ አንተ ስለእኔ ትቀናለህን?” (ዘኊል. 11፥29) በማለት፣ ታላቁ መገለጥ ለሕዝቡ ኹሉ እንዲገለጥና እንዲያገኛቸውም አብዝቶ ተመኘ። እጅግ የሚደንቀው ነገር የዘኊልቅ መጽሐፍን ሲጽፍ እንኳ፣ እጅግ የበዛውን ትውልዶች በመቁጠር ሲደክም ትልቁ ዓላማው ሊያርፍበት ያለውን ዋናውን መሲህ ፍለጋ ነበር። እርሱን ስላላገኘም በብዙ ፍለጋ ውስጥ ማለፉን እናስተውላለን።
    አንድ አባት ይህን እውነት በመጽሐፋቸው እንዲህ ብለው ገልጠዋል፦

Saturday, 4 August 2018

ለ'ኔ ስትል "አርደህ"



"እኔ ቀናተኛ" ስትለኝ አምላኬ፤
እንዴት ትቀናለህ? ብያለሁ ሞግቼ፤
ግና ...

Wednesday, 1 August 2018

“ … ይጸለይባችኋል” ፤ እንዲህም ደግሞ መች ነው የተጀመረው?

Please read in PDF
(ምነው ነውራችን አላልቅ አለ?)
   ከአንድ ወዳጄ ጋር በሥራ ምክንያት ተገናኝተን የቤተሰቡን የውርስ ጉዳይ ያማክረኛል። ሁሉም የተትረፈረፈ ሃብት አላቸው። የአባታቸው ውርስ ደግሞ የእነርሱን ይበልጣል። ሕጋዊውን መንገድ ከተጨዋወትን በኋላ መላ ቤተሰቡ ተማምነው ለታላቅ ወንድማቸው ውክልና ይሰጡትና ንብረቱ በየድርሻቸው በታላቅ ወንድማቸው እጅ እንዲተዳደር ይደረጋል። በሰላም ነገሩ ተቋጨ። ነገሩ ከተጠናቀቀ ከሦስት ወር በኋላ ግን የቤቱ አራተኛው ልጅ (ከሌሎቹ ይልቅ እጅግ ብዙ ሃብትና ተሰሚነት አለው) እኔው ያለሁበት ድረስ ይመጣል። ለካ፥ ከመካከላቸው አምስተኛው ልጅ ከአራተኛው ታላቅ ወንድሙ ጋር ተጋጭቶ በጠብ ይፈልገዋል።

Tuesday, 24 July 2018

“የኹለቱ ሲኖዶሶች” ነገረ ዕርቅ


     አንድ ሰው ከወንድሙ ጋር ተጣልቶ ሳይታረቅ ለጸሎት ወደ እግዚአብረር ፈፎሐሔሔር ቢቀርብ፣ በራሱ የቀረቀረውን በር መልሶ የማንኳኳት ሥራን ነው የሚሠራው፤ ይህ ደግሞ ከንቱ ልፋትና ድካም ነው። በጠብና በቅያሜ የሚኖር ሰውም ኾነ ቤተክርስቲያን ጸሎት የሚሰማውን የሰማይ ደጅና በርን የዘጋው ራሱ በራሱ ላይ ነው። ይቅር ለመባል፣ ይቅር ማለት የሚቀድም ከኾነ፣ ይቅር አልልም በማለታችን ይቅርታችንን የገፋነው እኛው እንጂ ይቅር ባዩ ጌታ አይደለም። በጠብና በበቀል፣ በጥላቻም መኖር ጸሎትንና በእግዚአብሔር ፊት የምናደርገውን ማናቸውንም “መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ያረክሳል”። ጌታችን ኢየሱስ ለዚህ ነው፦ “ስለዚህ መባህን በመሠዊያው ላይ ለእግዚአብሔር በምታቀርብበት ጊዜ ወንድምህ የተቀየመብህ ነገር መኖሩ ትዝ ቢልህ፣ መባህን በዚያው በመሠዊያው ፊት ተወው፤ በመጀመርያ ሄደህ ከወንድምህ ጋር ተስማማ፤ ከዚያም ተመልሰህ መባህን ለእግዚአብሔር አቅርብ” (ማቴ. 5፥23-24) (ዐዲሱ መደበኛ ትርጉም) በማለት፣ ወንድምን አለመቆጣት፣ አለመሳደብ፣ አለመራገም፣ አለመናቅ፣ አለመግደል ብቻ ሳይኾን፣ ከወንድማችን ጋር የማንስማማበትና የማንግባባበትም ነገር ሊኖረን እንደማይገባ ጭምር የነገረን። መሥዋዕትና ማናቸውም መንፈሳዊ ነገር ከማከናወናችን በፊት፣ በመካከላችን ያለውን አለመስማማት፣ ክፉ መንፈስ፣ ቅራኔ፣ ቅያሜ ማስወገድ ይገባናል፤ በምትኩ መስማማት፣ ይቅርታ ፍቅር ምሕረት ማድረግ ይገባናል።

Wednesday, 18 July 2018

በሕማሙና በትንሣኤው ዙርያ የነበሩ ምስክሮች (ክፍል ኹለት)

2   ሴፍጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ወቅት እጅግ አስደናቂና አስገራሚ ክስተቶች ተከስተዋል፤ አንክድህም አብረንህ እንሞታለን ያሉቱ መከራና ፍርሃት ፈቷቸዋል፤ ፈጽመው ወደ ኋላ አፈግፍገዋል፤ ምንም እንኳ መከራ እንደ ሚመጣ ጌታችን አስቀድሞ የተናገረ ቢኾንም፣ በሥጋ ጉልበት ሊቋቋሙ በማሰባቸው ተሸንፈዋል፤ ጴጥሮስ በፈሪ ሰይፉ ጆሮ ሲቆርጥ ተስተውሏል።

Wednesday, 11 July 2018

ደቂቀ እስጢፋኖሳውያንና የ“ዲያቆን” ዳንኤል ክብረት የክፋት ሸፍጥ (የመጨረሻ ክፍል)

ሰው ታርዶ ብርሃን ከሰማይ ይወርዳልን?

  ተአምረ ማርያም እስጢፋኖሳውያን በንጉሡ ዘርዓ ያዕቆብ በመታረዳቸው ምክንያት ብርሃን መውረዱን ሲናገር እንዲህ ይላል፦
  “... እኒህን ከሐዲያን ከወገሯቸው ወዲህ ሠላሣ ስምንት ቀን በሆነ ጊዜ  ... ስለእናቱ ስለእመቤታችን ስለከበረ መስቀሉም የክርስቶስ መስቀል በሚከበርበት በመጋቢት ዐሥር ቀን ሰኞ ሌሊት እግዚአብሔር ድንቅ ተአምር አደረገ። በንጉሡ ድንኳን ላይ ፍጹም ብርሃን ወጥቶ እንደ ጎርፍ ፈሰሰ። ... የዚያ ብርሃን መልኩም እንደ እሳት ላንቃ ይመስላል። ነገር ግን አያቃጥልም ነበር። ወደ ሰውም በቀረበ ጊዜ ፊት ያበራል የብርሃኑም መታየት ልቡናን ደስ ያሰኛል ...” (ተአምረ ማርያም)[1]
  “… ከዚህ በፊት ከቤተ ክርስቲያን የተቀበሩትን ቅዱሳንም (ከመቃብር) አውጥተው በድንጋይ እንዲወግራቸው አዘዘ።  ወታደሮቹ እንዳዘዛቸው አደረጉ። በዚህ ምክንያት በመንግሥቱ ብሔሮች ሁሉ ትልቅ ፍርሃት ሆነ። ንጉሡ ለነዚህ ጥቂት መንጋ በሆኑ በቅዱሳን ዘንድ በቀር ክህደቱን እንደ ከሐዲው እንደ ዲዮቅልጥያኖስ አልገለጠም። “እግዚአብሔር አማሌቅን ዘር ማንዘራቸውን በድብቅ እጅ ይመታቸዋል” ተብሎ እንደ ተጻፈው እግዚአብሔር ሲመታ አይገልጽም። እግዚአብሔር እንዴት እንደ መታ (እነሆ)፤ ቅዱሳኑን ባሠቃያቸው ጊዜ እንደ ሚበተን የወናፍ ምድጃ እሳት ዓይነት እሳት አመጣ፤ በድንኳኑ ላይም ታየ፤ እሱና ሠራዊቱ ግን ተደስተው፥ “ብርሃን በእኛ ላይ ወረደ” አሉ። ከሊቃውንቱ አንዳንዶቹ፥ “ብርሃን አይደለም፤ ይህ እንዲያውም የእግዚአብሔር የቁጣው ምልክት ይመስላል። ይኽ ሰው የእግዚአብሔርን ባሮች ስላሠቃያቸው በላያችን ላይ የሚመጣብንን መቅሠፍት እንዴትና ምን (እንደሚሆን ምን) እናውቃለን?” አሉ።” [2]