Sunday, 29 May 2016

ለካ በተጣዱበት የሚሞቁ ምርጥ አርቲስቶች አሉን?¡¡¡


    አውቃለሁ ፤ ክርስትና የመገለጥ ጉዳይ እንጂ የእውቀት ጉዳይ አይደለም፡፡ ይህን የምለውም በግኖስቲካዊ አቋም ዕውቀትን ከሚያመልኩ ጐን በመሰለፍ ወይም አምርረው ከሚጠሉትም ጐራ ራሴን በመደመር አይደለም፡፡ ክርስትና በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ የሆነውን ቤዛነትና ውጅት ማመንና ይህንንም መንፈስ ቅዱስ በፍጹም መገለጥ የሚያስተምረን ሕያው እውነት ነው፡፡ ይህም የሚሆነው ላመኑትና ለተቀበሉት ብቻ ነው (ዮሐ.1፥12)፡፡

  ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን አምኖ መቀበል ማለት፥ በሕይወታችን ፣ በትዳራችን ፣ በሥራችን ፣ በሁለንተናችን እርሱን ማመንና በተገለጠ ቅዱስ ሕይወት እርሱን ጌታችንን በኑሮአችን መመስከር ማለት ነው፡፡ ጌታ ኢየሱስን ለማመንና ለመቀበልም ሆነ ለማገልገል ፍጹም መሞት ያስፈልጋል፡፡ በትክክል ሳንሞት በትክክል መኖር አንችልም ፤ በትክክል ሳንኖርም በትክክል መሞት አንችልም፡፡ መስቀል ባልፈተነው ጉብዝና እንደመኖር ባዶ ክርስትና የለም፡፡

Monday, 23 May 2016

“የ‘ፌስቡክ’ ትውልድ” (ክፍል አንድ)

please read in PDF

    

 ማኅበራዊ ድኅረ ገጾች ለብዙ ዓመታት የተለያዩትን ቤተሰቦች ፣ ዘመዶች ፣ ወገኖች የመገናኘት ምክንያት ሆነው፤ ለንግዱ ማኅበረሰብ ሥራዎቻቸውን በቀላሉ እንዲያስተዋውቁና እንዲያሻሽጡ ፤ ለተጠቃሚውም ዝቅተኛ የገበያ ዋጋ ፣ በጥራትና በዋጋ የተሻለውን ለመምረጥ ፤ በማኅበረሰቡና በአገራት መካከል ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ግንኙነትን ለመፍጠር ፤ የአንዱን ማኅበረሰብ መልካም እሴት ለሌላው ለማስተላለፍ ፣ ለብዙዎች የሥራ እድል ለመፍጠር ፣ ስለተለያዩ ነገሮች የተለጠፉ “አስፈላጊ” የሆኑ መረጃዎችን “ለመጠቀም” ፤  “ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥” (ማቴ.24፥14) ተብሎ እንደተነገረ፥ ወንጌልን “ለዓለሙ ሁሉ” ለማሰራጨትና ለሌሎችንም ፋይዳዎች ያስገኙትን ያህል የዚያኑ ያህል (ምናልባትም በሚበልጥና በከፋ ሁኔታ) አሉታዊ ጎናቸውም እጅግ ሰፊና አሳሳቢ ነው፡፡

Saturday, 14 May 2016

ብርሃን ትሆኑ ዘንድ


ያ አሮጌው አዳም ፍጥረትን አስረጀ
በልዞ ቸክኮ  ፤ በኃጢአት ሸለቆ ዘመናትን ፈጀ
አልታዘዝንምና፦ እኛንም አገኘ ፤

Tuesday, 10 May 2016

“ለዚህም ነገር እኛ ሁላችን ምስክሮች ነን” (ሐዋ.2፥32)

   
   ደቀ መዛሙርት የተጠሩለት ዋና ዓላማ አንድና ግልጥ ነው፡፡ “መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥” (1ቆሮ.15፥3-4) የሚለውን ሕያው እውነት ለዓለሙ ሁሉ ማወጅና መመስከር ነው፡፡
   
          በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት መንፈስ ቅዱስ ገና ከጽንሰቱ ጀምሮ አብሮ ነበር (ሉቃ.1፥35) ፤ በአገልግሎቱ ጅማሬም መንፈስ ቅዱስ ፍጹም አልተለየውም (ሉቃ.4፥17) ፤ ሲጠመቅም እንደርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ ታይቷል (ማቴ.3፥16) ፤ በትንሣኤውም እግዚአብሔር የሞትን ጣር አጥፍቶለት (ሐዋ.2፥24) እንደቅድስና መንፈስ (ሮሜ.1፥4) ከሙታን መካከል ተነስቷል ፡፡

Thursday, 5 May 2016

እውን ከጾምን ምንን ይሆን የተራብነው?


ጌታ ኢየሱስ ከጾመም በኋላ እንደሰውነቱ ተርቧል፡፡ “አርባ ቀን ከዲያብሎስ ተፈተነ። በነዚያም ቀኖች ምንም አልበላም፥ ከተጨረሱም በኋላ ተራበ” (ሉቃ.4፥2) እንዲል፡፡ ጾም የዝግጅት ጊዜ ነው ፤ የዝግጅት ጊዜም ስለሆነ ጌታ ወደአደባባይ አገልግሎት ከመውጣቱ በፊት ጾምን ጾመ፡፡ ከጾመ በኋላ ደግሞ መራቡን እናስተውላለን፡፡ በዓውዱ ያስተዋልን እንደሆን የተራበው መብልን ይመስላል፡፡ ዋናውና ትልቁ የጌታችን ረሃብና ጥም  ምግብና መጠጥ እንዳልሆነ ግን ቅዱስ ወንጌልን ስናጠና እናስተውላለን፡፡
   በአንድ ወቅት በሰማርያ፥ ደቀ መዛሙርቱ ምሳን ሊገዙ ወደከተማ ሄደው ቆይተው፥ ምሳን ገዝተው ሲመለሱ ጌታ ኢየሱስ ከአንዲት ውኃ ልትቀዳ ከመጣች ሴት ጋር ሲያወራ አገኙት፡፡ በአይሁድ ልማድ አንድ ረቢ (ወንድም ቢሆን) ከሴት ጋር (ሚስቱንም ቢሆን) በመንገድ ላይ አያናግርምና እርሷን ያውም ሳምራዊትን ሴት በማናገሩ ደቀ መዛሙርቱ ተደነቁ፡፡ ምሳ እንዲበላ በለመኑት ጊዜ “እርሱ ግን፦ እናንተ የማታውቁት የምበላው መብል ለእኔ አለኝ አላቸው” (ዮሐ.4፥32)፡፡ እነርሱ ከመምጣታቸው በፊት ከሴቲቱ ጋር የአዲስ ኪዳንን የአምልኮ መሠረታዊ ትምህርትን ሲያስተምራትና መሲሕነቱን እየነገራት ነበር፡፡ ከደቀ መዛሙርቱ አንዳቸውም ስለምን ከሴቲቱ ጋር እንደሚያወሩ ጌታንም ሆነ ሳምራዊቷን ለመጠየቅ የደፈረ አልነበረም፡፡

Friday, 29 April 2016

“ፋሲካ”ውን በኃጢአት ልንፈስከው ቀን ቀጥረን ይሆን?


እንኳን ለብርሐነ ትንሣኤው መታሰቢያ በዓል በሠላም አደረሳችሁ፡፡
      የእስራኤል ልጆች የብሉይ ኪዳኑን ፋሲካ በተለያየ ዘመን እንዴት እንዳከበሩት ስናስተውል እንዲህ የሚመስሉ ቁም ነገሮችን እናገኝበታለን፦
ü በሙሴ ዘመን፦ የመጀመርያው ፋሲካ እንዲፈጸም የተሰጠው ለሙሴ ሲሆን ይህም በፈርዖን ቤት የበኵር ልጅ ሲገደል፥ በቤተ እስራኤል ይህ መቅሰፍት እንዳይደርስና እንዲያልፋቸው (ፋሲካ ማለት ማለፍ ማለት ነውና) ይህም የዘለዓለም ሥርዓት እንዲሆናቸው ተሰጣቸው፡፡ (ዘጸ.12፥14) ለፋሲካው የሚቀርበው ጠቦት በግ “ነውር የሌለበት”(ዘጸ.12፥5) ነው፡፡ ይህ በግ የሚበላው በመራራ ቅጠል እርሾ ከሌለበት ቂጣ እንዲሆን ታዘዋል፡፡ በእነዚህ የበዓል ቀናት እርሾ ያለበትን ቂጣ የሚበላ፦ “ከመጀመሪያውም ቀን አንሥቶ እስከ ሰባተኛው ቀን እርሾ ያለበትን እንጀራ የሚበላ ነፍስ ከእስራኤል ተለይቶ ይጥፋ” (ቁ.15) የሚል ግልጥ ማስጠንቀቂያ አለ፡፡ ስለዚህም ከዚህና ከሌሎችም ማስጠንቀቂያዎች የእስራኤል ልጆች ራሳቸውን ይጠብቁ ነበር፡፡ (ዘኍል.9፥6)

Thursday, 28 April 2016

ትዝታዬ ሁነኝ


                                         Please read in PDF

ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት መታሰቢያ በዓል እንኳን አደረሳችሁ፡፡


ሁሌ እራገማለሁ የአይሁድን ጥላቻ
ጌታ ኢየሱስን …
ለምን ጠሉት? ብዬ ሙግት ማንሳት ብቻ
ለምን ነው ይሁዳ? ለምን ነው ጲላጦስ?

Sunday, 24 April 2016

ሆሳዕና - ንጉሥ ያለቀሰላት ከተማ (ሉቃ.19፥41)

Please read in PDF

“... ከተማይቱን አይቶ አለቀሰላት፥ እንዲህ እያለ፦ ለሰላምሽ የሚሆነውን በዚህ ቀን አንቺስ ስንኳ ብታውቂ፤ አሁን ግን ከዓይንሽ ተሰውሮአል። አንቺንም በአንቺም ውስጥ የሚኖሩትን ልጆችሽን ወደ ታች ይጥላሉ፥ በአንቺ ውስጥም ድንጋይ በድንጋይ ላይ አይተዉም፥ የመጐብኘትሽን ዘመን አላወቅሽምና።” (ሉቃ.19፥41-44)


    መጽሐፍ ቅዱስን በማስተዋል እንደመንፈስ ቅዱስ ተማሪ ቁጭ ብለን ስናጠና፥ ነቢዩ ኤርምያስ አልቃሻው ነቢይ መሆኑን እናስተውላለን፡፡ ኤርምያስን አልቃሻ ያሰኘው፥ የእስራኤልን መጥፋትና መማረክ ፤ የቤተ መቅደሱን መፍረስና የጐበዛዝቱን መውደቅ በተናገረ ጊዜ ሰሚ ማጣቱ ፤ የሕዝቡ አንገተ ደንዳናነት እጅግ ያበሳጨውና ያስለቅሰው ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት እጅግ ረጅም ጊዜ በማልቀሱ አልቃሻው ነቢይ ተብሎ ተጠርቷል፡፡ ነቢይ ሕዝብን ከእግዚአብሔር በአደራ ተቀብሏልና ሕዝቡ በነፍሱ ሳያርፍ፥ ሲቅበዘበዝ ፣ ሲንከራተት ... ሲያይ አብሮ መባዘኑ መንከራተቱ አይቀርም፡፡ እስኪመለሱም እጅግ በማዘን ይተጋላቸዋል ፤ በተመለሱም ጊዜ እጅግ ደስተኛ ነው፡፡ የነቢይ የዘወትር ደስታው የሕዝቡ በአምላኩ መንገድ መሆን ብቻ ነው፡፡   

Tuesday, 19 April 2016

በጋምቤላ ፤ በሜድትራኒያን ዳርቻ … የሆነው፥ ለእኛ የ“ንስሐ ግቡ” ደወል ይሆን?




“አባቶቻችሁም እንደ ነበሩ አንገተ ደንዳና አትሁኑ ፤ እጃችሁንም ለእግዚአብሔር ስጡ፥ ለዘላለም ወደ ተቀደሰው ወደ መቅደሱም ግቡ፥ ጽኑ ቍጣውም ከእናንተ እንዲመለስ አምላካችሁን እግዚአብሔርን አምልኩ። አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ ነውና፥ ወደ እርሱም ብትመለሱ ፊቱን ከእናንተ አያዞርምና ወደ እግዚአብሔር ብትመለሱ ወንድሞቻችሁና ልጆቻችሁ በማረኩአቸው ፊት ምሕረትን ያገኛሉ፥ ደግሞም ወደዚህች ምድር ይመለሳሉ።” (2ዜና.30፥8-9)


    ከወደጋምቤላ እናት እስካዘለችው ልጇ ድረስ ተቀልታ በጠቅላላ ከ148 ሰዎች መታረዳቸውን ሰምተን ጆሮዋችን ሳያባራ፥ ከወደሜድትራኒያን ባሕር ዳርቻ ደግሞ ትውልደ ኢትዮጲያውንና ኤርትራውያን ይበዙበታል በተባለ የስደተኞች የባሕር ጉዞ ጀልባ ተገልብጦ ከ400 በላይ ሰዎች መሞታቸውን ተረዳን፡፡ የዛሬ ዓመት ገደማ ኢትዮጲያውያን በዚሁ በሜድትራኒያን ባሕር ዳርቻ በሰው በላው አይ ኤስ አይ ኤስ ዜጎቻችን እንደዋዛ እንደበግ ታርደው ደማቸው በከንቱ ከባሕር ጋር ተቀላቀለ፡፡

Sunday, 17 April 2016

ኒቆዲሞስ - ከውኃውና ከመንፈሱ የመወለድ ምስጢር (ዮሐ.3፥5)


“እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም።” (ዮሐ.3፥5)

   ኒቆዲሞስ የማታ ተማሪ ቢሆንም መምሕር ተብሎም ተጠርቷል ፤ ምናልባት ቀን ቀን ሕዝብ በተሰበሰበበትና ጌታን ዙርያውን ሕዝብ በከበበበት ሁኔታ እንደልብ ለመወያየት ስለማይመች ወይም በማታው ክፍለ ጊዜ በደንብ እንወደደው ሊያወራውና ከእርሱ ሊማር ወይም የአይሁድ አለቃ ስለሆነ በቀን መምጣትን ስለፈራ ሊሆን ይችላል፥ ሌሊቱን በቋሚ ተማሪነት በመምጣት የተጋው፡፡ ባለ ሥልጣን እንደመሆኑ መጠን ሰው ሳይልክ ራሱ መምጣቱ ሊማር ፤ ሊረዳ ከልቡ መውደዱን ፤ የመንፈስ ጥማትም ያለበት መሆኑን እናስተውላለን፡፡ ከጌታ ለመማር እርሱ ድካምና ዝለት ፤ ሌሊትና ቀን የማይፈራረቅበት የዘላለም መምህር ነው፡፡ ሲያስተምር በቅንነት ነው፡፡ ከታወቁ ሊቃውንትና ፕሮፌሰሮች የሚማሩ እጅግ ይደነቃሉ ፤ ከእርሱ የሚማሩ ግን እጅግ የተወደዱ ናቸው፡፡

Friday, 15 April 2016

አገርም፥ ይህን ያህል ይዘነጋል ለካ!




  መርሳት የተፈጥሮ ባህርያችን ነው ፤ ነገር ግን ጤነኞችና ኃላፊነት የሚሰማን ከሆነ ለዘወትር ልንዘነጋቸው የማይገቡን ነገሮች አሉ፡፡ በጦር ሜዳ ያለ ወታደር ትጥቅና የጦር መሣርያውን ፣ በሙሽርነት ያለች ሴት መጌጥና መዋብን ፣ በበሽተኞች የተከበበ ዶክተርና የሕክምና ባለሙያ ስለሚያክምባቸው የሕክምና መሣርያዎች ፍጹም ሊዘነጉ ከማይችሉ ጥቂት ነገሮች መካከል ናቸው፡፡ እነዚህንና ተመሳሳይ ነገሮችን መርሳት በሕይወት ጭምር አላስፈላጊ ዋጋ ያስከፍላሉ፡፡
   ከምንም በላይ ደግሞ ሕዝብን ለማገልገል በኃላፊነት የተቀመጥን ሰዎች ዘወትር ልመናችን እንደንጉሥ ሰሎሞን ብዙ ሃብትና ብዕል እንዲሰጠን ከመመኘት ይልቅ ሕዝቡን መምራት የሚያስችለንን ማስተዋልና ጥበብን እንዲሰጠን ቢሆን መልካም ነው፡፡ ሰሎሞን ይህንን ስለለመነ (1ነገ.3፥11)፥ “እግዚአብሔርም ለሰሎሞን እጅግ ብዙ ጥበብና ማስተዋል በባሕርም ዳር እንዳለ አሸዋ የልብ ስፋት ሰጠው።” (1ነገ.4፥29) ብሎ ቃሉ ይነግረናል፡፡ ልበ ሰፊነት ብዙ የሚመረምርና የሚያሰላስል ልብ ስለሆነ በዝንጋኤ የማይጠቃ አስተዋይ ልብ ነው፡፡

Sunday, 10 April 2016

ገብር ኄር - ለክርስቶስ ባሮች እንጂ ሎሌዎች አይደለንም!

    
  “ገና ያልተሰናሰናለው” ዘመናዊው መናፍቅነት የሆነው፥ ድኅረ ዘመናዊነት ወጣቱን ትውልድና “አዳዲሶቹን አማኞች” እያነሆለለበትና ኃጢአትን ያለገደብ ለማለማመድና ለማስፈጸም ከሚጠቀምበት አንዱ ማቀንቀኛ ሃሳቡ፥ “ሰው ነጻ ፍጡር ፤ ለማንም የመገዛት ግዴታ የለበትም ፤ ተገዝቶም አያውቅም” የሚል የጸና አቋም አለው፡፡ ይህ አባባል ሁለት ነገሮችን ሊናገሩበት ያሰቡ ያስመስላቸዋል ፤ (1) ድኅረ ዘመናዊነትን በልካቸው ለብሰው የታዩት አብዛኛዎቹ ምዕራባውያን ከፈሪሃ እግዚአብሔር ተፋተው “በፊታቸው መልካም መስሎ የታያቸውን በማድረግ፥ ለምናደርገው ነገር ሁሉ ኃላፊነቱን የፈጠረን ይውሰድ የሚል ኅሊና ቢስ ምክንያት ሲያቀርቡ ፤ (2) እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ሲፈጥረው የሰጠውን የምርጫ ነጻነት አጣመው ይተረጉሙታል፡፡

Wednesday, 6 April 2016

... የዋጠውን እንመነው!



አልማዝ ወርቅ እንቁውን፣ በኲራቱ ያደበሰ፤
ዘረ አዳምን አስጎንብሶ ፣ ብርታት አቅሉን ያፈረሰ፤

Sunday, 3 April 2016

ደብረ ዘይት - ጌታ ይመጣል!



     መናፍቃን ከሚክዷቸው የክርስትና መሠረተ ትምህርት አንዱ የክርስቶስን በክበበ ትስብእት ፤ በግርማ መለኮት ዳግመኛ መምጣት ነው፡፡ የክርስቶስ ዳግም መምጣት ትምህርት ክርስትናና አስተምኅሮው የተመሠረተበትና የቆመበት ዋና ዓለቱ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የዳግመኛ መምጣትን ትምህርት ስናነሳ በአብሮነት የሙታንን ትንሣኤ ትምህርት በአንድነት ማንሳታችን የግድ ነው፡፡ ሁለቱ ትምህርቶች ሰፋፊና በየራሳቸው መቆም የሚቻላቸው ቢሆኑም፥ ተያያዥና የማይነጣጠሉ ዋና ዓምዶች ናቸው፡፡
       ቅዱስ ሐዋርያ ጳውሎስ እንዲህ ይላል፦
“በጌታ ቃል የምንላችሁ ይህ ነውና፤ እኛ ሕያዋን ሆነን ጌታ እስኪመጣ ድረስ የምንቀር ያንቀላፉቱን አንቀድምም፤ ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን። ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ።” (1ተሰ.4፥15-18) (ለአጽንዖት የተሠመረበት የእኔ ብቻ ነው)

Sunday, 27 March 2016

መፃጉዕ - ለአገሬ፥ ሰው የሚሆንላት ማን ይሆን!?

    
 ዜመኛው ቅዱስ ያሬድ የዓቢይን ጾም ሳምንታት በሰየመበት ስያሜው፥ ይህን ሳምንት መፃጉዕ ብሎ ሰይሞታል፡፡ ትርጓሜው በቁሙ ሲፈታ “ጐባጣ” ማለት እንደሆነ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ(አለቃ) መጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በሚለው መዝገበ ቃላቸው ገጽ 605 ላይ ፈትተውታል፡፡ ለስያሜው መሰጠት ምክንያቱ ደግሞ ቅዱስ ያሬድ የአጽዋማቱን ሳምንታት ስያሜዎች ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲወርሰው አድርጎታል፡፡ ይህ ስያሜም በምን ምክንያት ከጌታ ጋር እንደተገናኘ ሲናገር እንዲህ አለ፦
“በሰንበት ቀን ኢየሱስ ታላላቅ ተአምራትን ያደርግ ነበር፡፡ ከዚህ ሁሉ የሚበልጥ ያደረገውንም እናገራለሁ፡፡ ጭቃ ደህናውን ዓይን ያጠፋል፣ እርሱ ግን በምድር ላይ ተፍቶ ጭቃ አድርጎ ዕውር ሆኖ የተወለደውን አዳነ፡፡ ይህ ግሩም ምስጢር ነው፡፡”