Wednesday, 28 September 2016

የጳጳሱና የሰባክያኑ ቤተ ክርስቲያንን “መለካዊ” የማድረግ ሃሳባቸው እስከምን ድረስ ነው?!

Please read in PDF      

          ነቢየ እግዚአብሔር ኤርምያስ በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች ዘንድ “አልቃሻው ነቢይ” ተብሎ ይጠራል፡፡ ይህንንም ስያሜ ያገኘበት ዋናው ምክንያት፥ ሕዝቡ በኃጢአትና በነውር ምድሪቱን እጅግ በማርከሳቸውና ፊታቸውን ወደንስሐ ዘወር እንዲያደርጉ፥ ከእነርሱ ጋር እየተራበና እየተጠማ በመካከላቸው ሆኖ አዘውትሮ ቢናገራቸውም፥ እስራኤል ሊሰሙት ካለመውደዳቸው ባሻገር አጥብቀው ስለተቃወሙትና ሊቀበሉት ፈጽመው ስላልወደዱት ነው፡፡
    በዚህም ምክንያት በጥልቅ ሐዘን መዋጡን፥
    “አንጀቴ! አንጀቴ! ልቤ በጣም ታምሞአል፥ በውስጤም ልቤ ታውኮብኛል፤ ነፍሴ ሆይ፥ የመለከትን ድምፅና የሰልፍን ውካታ ሰምተሻልና ዝም እል ዘንድ አልችልም፡፡ … ሕዝቤ ሰንፈዋልና አላወቁኝም ሰነፎች ልጆች ናቸው፥ ማስተዋልም የላቸውም፤ ክፉ ነገርን ለማድረግ ብልሃተኞች ናቸው፥ በጎ ነገርን ማድረግ ግን አያውቁም፡፡”፤ (ኤር.4፥19-22)፤ “ተወግተው ስለ ሞቱ ስለ ሕዝቤ ሴት ልጅ ሰዎች ሌሊትና ቀን አለቅስ ዘንድ ራሴ ውኃ፥ ዓይኔም የእንባ ምንጭ በሆነልኝ! ሁሉም አመንዝሮች፥ የአታላዮች ጉባኤ ናቸውና ሕዝቤን እተዋቸው ዘንድ ከእነርሱም እለይ ዘንድ በምድረ በዳ የመንገደኞች ማደሪያን ማን በሰጠኝ? ምላሳቸውን ስለ ሐሰት እንደ ቀስት ገተሩ፤ በምድር በረቱ ነገር ግን ለእውነት አይደለም፤ ከክፋት ወደ ክፋት ይሄዳሉና እኔንም አላወቁምና፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ ወንድምም ሁሉ ያሰናክላልና፥ ባልንጀራም ሁሉ ያማልና እናንተ ሁሉ ከባልንጀሮቻችሁ ተጠንቀቁ፥ በወንድሞቻችሁም አትታመኑ፡፡ ሰውም ሁሉ ባልንጀራውን ያታልላል በእውነትም አይናገርም፤ ሐሰትን መናገርንም ምላሳቸው ተምሮአል፥ ክፉንም ለማድረግ ይደክማሉ፡፡”(9፥1-5)፤ “እረኞች ሰንፈዋልና፥ እግዚአብሔርን አልጠየቁትምና አልተከናወነላቸውም፥ መንጎቻቸውም ሁሉ ተበትነዋል፡፡”(10፥21)፤ “ስለ ነቢያት፤ ልቤ በውስጤ ተሰብሮአል አጥንቶቼም ሁሉ ታውከዋል፤ ከእግዚአብሔር የተነሣ ከቅዱስ ቃሉም የተነሣ የወይን ጠጅ እንዳሸነፈው እንደ ሰካራም ሰው ሆኛለሁ፡፡ ምድር ከአመንዝሮች ተሞልታለችና፥ ከመርገምም የተነሣ ምድር አልቅሳለች፤ የምድረ በዳ ማሰማርያ ደርቆአል፤ አካሄዳቸው ክፉ ነው፥ ብርታታቸውም ቅን አይደለም፡፡ ነቢዩና ካህኑም ረክሰዋልና፥ በቤቴም ውስጥ ክፋታቸውን አግኝቻለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡” (23፥9-11)
የሚለው የነቢዩ ንግግር የሚያየው የእስራኤል ክፋት ምን ያህል እንዳቆሰለውና እንዳሳዘነው በትክክል ይገልጠዋል፡፡

Tuesday, 20 September 2016

በዘመን መለወጫ የተቀማጠለው ንጉሥ (የመጨረሻ ክፍል)

  please read in PDF

ልንመርጥ የምንችለው አንድ መንገድ ብቻ ነው፤ ከኃጢአትና ከጽድቅ መንገድ አንዱን፡፡ ከሁለቱ አንዱን እንጂ ለሁለቱም ማመቻመች አንችልም፡፡ “ከኃጢአት ጋር እየተጋደላችሁ ገና ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ አልተቃወማችሁም፤” (ዕብ.12፥4) የሚለው ቃል በእውነት ላይ እስከመጨረሻ አለመጽናትንና አለመጨከንን የሚያሳይ ነው፡፡ ለእውነት ከቆምን እስከሞት ድረስ እንጂ ሁለቱን ለማደላደል መሞከር ከውርደት አያድነንም፡፡
    የሳሙኤልን መጽሐፍ የጻፈው ጸሐፊ፥ በንጉሥ ዳዊት ሕይወት የሆነውን ውድቀት ሁሉ ምንም ሳያዛንፍ ነው፡፡ አስቡ! የነቢዩ ሳሙኤልን ሕይወት፥ “እነሆኝ በእግዚአብሔርና እርሱ በቀባው ፊት መስክሩብኝ የማንን በሬ ወሰድሁ? የማንንስ አህያ ወሰድሁ? ማንንስ ሸነገልሁ? በማንስ ላይ ግፍ አደረግሁ? ዓይኖቼንስ ለማሳወር ከማን ጋር እጅ ጉቦ ተቀበልሁ? እኔም እመልስላችኋለሁ፡፡ እነርሱም፦ አልሸነገልኸንም፥ ግፍም አላደረግህብንም፥ ከሰውም እጅ ምንም አልወሰድህም አሉ፤” (1ሳሙ.12፥3-4) በማለት ገልጦታል፡፡ እንዲሁ የዳዊትን ደካማና ኃጢአተኛ ሕይወት ሳያቅማማ ነው የገለጠው፡፡

Wednesday, 14 September 2016

... አዲስ ዘመን የለም



ቢግተለተል ዕድሜ፥ ምን ቢረዝም ዘመን፤
ተቆጥሮ ተሰልቶ፥ ቢሰጠን ብዙ ቀን፤

Friday, 9 September 2016

በዘመን መለወጫ የተቀማጠለው ንጉሥ (ክፍል አንድ)


Please read in PDF

እንኳን ለንስሐ የሚሆን ዘመን  ተጨመረላችሁ!!!
     ቅምጥልነትን፥ ቅዱስ ጳውሎስ “ቅምጥሊቱ ግን በሕይወትዋ ሳለች የሞተች ናት” (1ጢሞ.5፥6) በማለት ይገልጠዋል፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት መሞትን በሕይወት ቆሞ መሄድ አይተካውም፡፡ መንፈሳዊ ሞት ወደር የለሽ እጅግ አስጨናቂ ሞት ነው፡፡ ቆሞ በመሄድ ማማር የለም፤ በቁም “በውጭ አምረው የሚታዩ” ሁሉ ደመ ግቡዎች አይደሉም፤ ውስጣቸው “ርኩሰትም ሁሉ የተሞሉ በኖራ የተለሰኑ መቃብሮችን ሊመስሉ ይችላሉና”፤ (ማቴ.23፥27)፡፡ እንዲህ ያሉ ሰዎች በሕይወት የሞቱና ሕያውና የሚያድን ድምጽ መስማት የሚያስፈልጋቸው ናቸው፡፡
     ጌታችን “ሙታናቸውን እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው፤ አንተስ ሄደህ የእግዚአብሔርን መንግሥት ስበክ” (ሉቃ.9፥60) በማለት የተናገረው፥ በመንፈስ ሙት የሆኑ በሥጋ ሙት የሆኑትን ሊቀብሩ እንዳሉና በመንፈስ ሕያው የሆነ ግን የእግዚአብሔርን መንግሥት በብርታት ማገልገልና መስበክ እንዳለበት አጽንቶ ሊናገር ወዶ ነው፡፡ አስተውሉ! ጥቂት ቅምጥልነት ለምን አይነት መንፈሳዊ ሞት አሳልፎ ሊሰጠን እንደሚችል፡፡
   ንጉሥ ዳዊት ሁሉንም “ጠላቶቹን” ቢያሸንፍም፥ አሞናውያንን [1] ግን ገና አላሸነፈም ነበር፤ (2ሳሙ.10፥19)፡፡ እኒህ የቀሩ ጠላቶች ቢኖሩትም ግን፥ “እንዲህም ሆነ፤ በዓመቱ መለወጫ ነገሥታት ወደ ሰልፍ በሚወጡበት ጊዜ፥ ዳዊት ኢዮአብን ከእርሱም ጋር ባሪያዎቹን እስራኤልንም ሁሉ ወደጦርነቱ ሰድዶ ለራሱ ግን በኢየሩሳሌም ቆየ፤” (2ሳሙ.11፥1) አመሻሽ ላይ በዚያ ምቹና ተስማሚ ሰገነት ላይ (1ሳሙ.9፥25) ዳዊት ይመላለስ ነበር፡፡ በሌላ ንግግር ወደዳዊት ሕይወት ቅምጥልነት ሰተት ብሎ ገባ ማለት ነው፡፡ “በልክ መዝናናት” አንድ ነገር ነው፤ ለሥጋዊ ተድላና ለቅምጥልነት ተዘልሎ መቀመጥ ግን ራስን በወጥመድ ውስጥ የማስገባት ያህል እጅግ አደገኛ ነው፡፡

Sunday, 4 September 2016

የኢትዮጲያ “መካከለኞች” ወዴት ናቸው?

Please read in PDF     

       ቺቸሮ “አለመግባባት መፍትሄ የሚያገኘው በሁለት መንገዶች በውይይት ወይም በኃይል ነው፡፡ የመጀመርያው የሰው ባሕርይ ሲሆን ሁለተኛው የአራዊት ነው” ይላል፡፡ ባለመታደል ሁላችንም ሁለተኛውን መረጥን፡፡ ማሸነፍ እንጂ መሸነፍን ያለመቀበል እንደባህል አድርገን በመያዛችንና በሃገሪቱ የፖለቲካ ልምድ ካለመኖር ጋር ተዳምሮ የኢትዮጲያ ተራማጆች ኃይልን መርጠው በመንቀሳቀሳቸው የደም መፋሰሱንና የጥፋቱን መጠን በማባባስ ለሃገር ግንባታ ይውል የነበረ ወጣት ለቅስፈት ተዳርጓል፡፡ (ሌ/ኰሎኔል ፍሥሐ ደስታ፤ አብዮቱና ትዝታዬ ፤ 2008 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ፤ ፀሐይ አሳታሚ ድርጅት)

       ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለ ማርያም “እርምጃ እንዲወሰድ ከማዘዛቸው” በፊትም ሆነ በኋላ፥ የሕዝብ ኩርፊያ አሁንም ጋብ ያለ አይመስልም፡፡ ሕዝብ እንደሚናጠቅ የአንበሳ ደቦል “በገዛ ወገኑ” [እርስ በራሱ] ላይ ያደባ ይመስላል፤ “መንግሥት ሆይ!  ችግር አለብህ፤ ተስተካከል” ለማለት እየሄደበት ያለው አቅጣጫና አንዳንዶች እንደሚሉት ሕዝቡን የሚመራው “ሦስተኛው አካል” ዓላማና ግቡ ምንም እንደሆነ በትክክል አለመታወቁ ነገሮች የበለጠ እንዲወሳሰቡ ያደረገ ይመስላል፡፡
     እርግጥ ነው፥ የአብዛኛው ሰው ስሜት ሲደመጥ፥ “ይኼ መንግሥት በቃው፤ ይውረድ” ይመስላል፡፡  ይህ አካሄዱ ግን ፍጹም ኢ መንፈሳዊነት ብቻ ሳይሆን ኢ ሰብዓዊነት፣ ኢ ሥነ ምግባራዊነትና ኢ ሞራዊነት የሰፈነበት መሆኑ ነገሩን አስጨናቂና እጅግ አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡ ምንድር ነው አስጨናቂና አሳሳቢ የሚያደርገው? ብንል፦
1.     ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ምን ሆነው? በማን ላይ ነው እርምጃ እንዲወሰድ አዝዣለሁ ያሉት? ከእርምጃው በፊት ማወያየትና ማነጋገር አይቀድምም ወይ? ምክር አይፈለግም ወይ? እርምጃ የመጀመርያ ደረጃ መቀራረቢያና መግባቢያ መንገድ ነው ወይ? ሕዝብን ማድመጥና ፍላጐቱን መጠየቅ አይገባም ወይ? በደፈናው ከመፈረጅ ጥንተ ምክንያቱን ማጥናት፤ መረዳት አይገባም ወይ? ወይም ለምንድነዉ መንግስት በፖለቲካ አቅጠጫ ማሸነፍ የተሳነው? የሚሉና ሌሎች ብዙ ጥያቄዎችን መምዘዝ ይቻላል፡፡

Saturday, 27 August 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና (ክፍል ሦስት)

በእኛ መካከልስ ምን ይመስል ነበር?
   ዘረኛነትን በተመለከተ ከአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ብንነሳ፥ ኢትዮጲያ ከሰማንያ አራት በላይ ብሔረሰቦች የሚኖሩባትና በተለያየ ብዙ ቋንቋዎችም የሚነጋገሩ ሕዝቦች ያሉባት አገር ናት፡፡ አንዱ አንዱን ለመብለጥ ምክንያት የሚመስሉ ብዙ ነገሮች አሉ፤ ሰዎች ከአንድነት ይልቅ በየራሳቸው ነገር ላይ ትኩረት ሲያድርጉ ሳያውቁት ሌላውን በመጻረር የሚቆሙበት ጊዜም ብዙ ነው፡፡ ሰዎችን ወደሌላ የክህደት መንገድ ለመምራት መጽሐፍ ቅዱስን ሲያጠኑ በዚያው የመጽሐፍ ቅዱስ አማኝ ሆነው የቀሩ ሰዎች ያሉትን ያህል፤ መጽሐፍ ቅዱስን ተጠግተው ለራሳቸው ምስክርነት እየፈለጉ በዘረኛነት ክፉ ኃጢአት የተያዙ ብዙ ናቸው፡፡
    መጽሐፍ ቅዱስን ተገን ተደርጐ የሚሠራ ኃጢአት እጅግ አስከፊ ኃጢአት ነው፤ በእኛ መካከል ያለው የዘረኛነት መንፈስ እንዲህ ያለ ነው ብንል ማጋነን አለበት አያስብልም፡፡ አንድ ሃይማኖት የተወሰኑ ወይም የአንድ ብሔር እስኪመስል ወይም እስኪባል ድረስ በመካከላችን የሚታየው ነገር አስነዋሪ ነው፡፡ ይህንን በአንድ ጽሑፍ፦
“ … አሁን አሁን ነገራችን እንደዖዝያን ለምጽ ሊሸፈንበት ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ ራሱ ችግሩም “አለሁ፣ አለሁ” ብሏል፡፡  የለህም ብንለውም ራሱን በራሱ ያስመሰክራል፡፡ ሙስናው ፣ የዘመድ አሠራሩ …ወዘተ አግጥተው ወጥተዋል፡፡” [1]

Monday, 22 August 2016

በአዲስ አበባ፥ ምነው በሰበበ “ሰላማዊ ሰልፍ” ሁከት አልተቀሰቀሰም?!

Please read in Pdf 
የኢዮአታምን ምክር የማይሰማ ሕዝብና መሪ መጨረሻው ጥፋት ነው!!!
     ትላንት ማምሻውን ስልኬ ከወደብዙ ቦታ በተደረገላት ጥሪዎች ስትንጫረር ነበር፡፡ ከ“ክፍለ አገር” እና ከውጪው ዓለም፡፡ “አዲስ አበባ ሰላም ዋለችን? ከመገናኛ ብዙኃን ምንም መረጃ አጣን? ምንም ሁከት ወይም ሰላማዊ ሰልፍ አልነበረም? ... ምንም ምን አልነበረም? ... ” የሚሉና ሌሎች ጥያቄዎችን የሚጠይቁ ወንድሞችና እህቶች፡፡
     ከዚህ የጥያቄ ግርፍ በኋላ ለረጅም ሰዓት ቆም ብዬ ማሰላሰል ጀመርኩ፡፡ ሰው ከሰላም ይልቅ “ሰላማዊ ሰልፍ” ለምን ተጠማ? ከጸጥታ ይልቅ ግርግርና ሁከት ለምን መረጠ? የማያስማማ፣ የማያነጋግር፣ የማያወያይ፣ ጅምር ላይ ሆነን ፍጻሜ መተለም የማያስችል ክፉ መንፈስ ከወዴት ይሆን የተጣባን? የቀደመው ዘመን ታሪክ ስለምን መማርያ አልሆነንም? ከዚህ ቀደም የ“ንጉሠ ነገሥቱን” ሥርዓት ሰለቸን ብለን፥ ከአርባ ዓመት በላይ “የመራንን” ንጉሥ አዋርደን፣ ከሰውነት ተራ አውጥተን፣ “ለባዕድ” የማይነፈገውን የቀብር ቦታ እንኳ ለ“ንጉሠ ነገሥቱ” ነስተን፣ ስም አጠራሩን አጥፍተን ... ወታደራዊውን መንግሥት “በእልልታ በሆታ” በራሳችን ላይ ሾምን፡፡
እርሱም የዘራነውን አሳጨደን፡፡

Thursday, 18 August 2016

በዓይናችን አይተን!

Please read in PDF


ተረት መች ሆነና ብልሐታዊ ንግርት፣
የምሰብከውና የምንዘምርለት፣
አጉል ፍልስፍና ጥበብ መሰል ነገር፣

Tuesday, 16 August 2016

የኢትዮጲያ የ“ማስተዋል” ጸሐይ ምነው አዘቀዘቀ?



Please read in PDF


መንግሥት ሆይ! እባክህ ከማሰር ፤ ከማጐር ይልቅ፥ ራራ! ይቅር በል! ማር!!!
     በምዕራቡ ዓለም በተደላደለ መኖሪያ ቤታቸው ተቀምጠው እንደሰበኩን፥ “ጨካኝ ፣ እብሪተኛ ፣ አምባገነን ፣ አረመኔ ፣ ጉበኛ ፣ ዘረኛ ፣ ሴሰኛ ፣ አድርባይ ፣ አፋኝ …” ያሉት ይህ የአገር ቤቱ መንግሥት ወረደ እንበል፤ ግን እኒህ ዲያስፖራ ፖለቲከኞችና ፈሪሳውያን ሃይማኖተኞች ያልመለሱልን ጥያቄ፥ “ማን እንዲመራን ነው ያቀዱት? ፣ ማንን ይሆን ያዘጋጁልን? እነርሱ ራሳቸው ከአውሮፓና ከአሜሪካ ሊመጡና ሊመሩን? ፣ ወይስ ከዚሁ አገር ቤት የሚያሰናዱልን ነገር ኖሮ ይሆን?”
     አንድ ሌላ ጥያቄ አለኝ? እኒህ “ዲያስፖራውያን የፖለቲካና የሃይማኖት ዲስኩረኞች” ለመሆኑ ስለአንድነትና ስለመንፈስ አንድነት ለማውራት በእውኑ ሞራሉና ብቃቱ አላቸው? በአንድ ነገር አምናለሁ ፤ የአገር ቤቱ መንግሥት ብዙ ነውር ፣ ዕድፍ ፣ ርኩሰት ፣ ልክፍት ፣ በደል … አለበት ፤ ይህን አምናለሁ፥ አልጠራጠርም፡፡ አንድ ብርቱ መከራከርያ ግን አለኝ፡፡ ከአገር ቤቱ መንግሥት ይልቅ “የአሁኑን የነውጥ እንቅስቃሴ እየመራ ያለው የዲያስፖራው ጐልማሳ” ግን ነውሩና ርኩሰቱ ከአገር ቤት መንግሥት ይበልጣል ባይ ነኝ፡፡

Monday, 8 August 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና (ክፍል ሁለት)

በአለም ላይ የነበረው ገጽታ
“ኹሉም የሰው ዘር የተፈጠረው በእኩልነት ነው”
(የነጻነት አዋጅ ፤ ሐምሌ 4 1776 ዓ.ም)
    Please read in PDF

በአለም ላይ የነበረው ገጽታ
“ኹሉም የሰው ዘር የተፈጠረው በእኩልነት ነው”
(የነጻነት አዋጅ ፤ ሐምሌ 4 1776 ዓ.ም)
     ይህ አለም አቀፍ አዋጅ በዘረኛ ጠባይና ድርጊት በሚከተሉ ሰዎች በግልጽ ከመሻሩና ከመጣሱም በላይ፥ በአለም ላይ ዘረኛነት በግልጥ የታየበት ጊዜም ብዙ ነው፡፡ በሥልጣኔ ከመጠቁት እስከ በሥልጣኔ ወደኋላ በቀሩት ሕዝቦች መካከል ከሚታይ ጥላቻ እስከትውልድ መደምሰስ የሚያደርስ የዘረኝነት ተክል በአለም ሁሉ ፊት  በቅሏል ፤ አብቧል ፤ ፍሬውም ሆምጣጤ ሆኖ በክፉ ምሳሌነቱ ታይቷል ፤ አሁንም ድረስ እየታየ ነው፡፡ ዘረኛነት ድንበር ሳይከለክለው በጸሐፍት፣ በባዕለ ሥልጣናት፣ በምሁራን [1] ፣ በጳጳሳት ፣ “ለምድር የከበዱ በሚባሉ ብዙ ሕዝቦች” ዘንድ ተገልጧል፡፡
       ሄሮዶተስ (Herodotus) [2] በሊብያ በረሃ ደቡብ ምዕራብ ጠረፍ ስለሚኖሩ ሕዝቦች ማንነት ሲናገር፥ “… ከአደገኛ አውሬዎችና ልዩና አስገራሚ ፍጥረታት ጋር የሚኖሩ ፣ ጭንቅላት የሌላቸው ፣ ዓይናቸው በደረታቸው ላይ የሚገኙ ወንዶችና ሴቶች ናቸው” [3] በማለት ለአፍሪካና አፍሪካዊ ማንነት የሰጠው ተፈጥሮን ተቃራኒ ንግር ነበር፡፡ [4] ጥቁር በመሆን ብቻ አፍሪካውያን ብቻ ሳይሆኑ፥ ሌሎች የእስያና የሌሎችም አህጉራት ሕዝቦች እጅግ ከባድ ውርደትና አጸያፊ ጥላቻን ለመቀበል ተገደዋል፡፡ ምናልባት ይህ እጅግ በራቀው ክፍለ ዘመን ፤ ሥልጣኔና አመለካከት ባልዳበረበት ዘመን ነው ብለን ብንሞግት እንኳ፥ አሻራው ሳይደበዝዝ በዚህ በዛሬው ጊዜ ፍንትው ብሎ ፤ በመካከላችንም ጭምር እናስተውለዋለን፡፡

Tuesday, 2 August 2016

“27 አባቴ” የሚባል አባት የለንም!

Read in PDF

    አባት የሚለውን ቃል አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላቸው ሲፈቱት፥ “የግብርና የክብር የማዕረግ ስም፡፡ አባት መባል በብዙ ወገን ስለኾነ ከግዜር ዠምሮ ያባትነት ሥራ ለሚሠሩ ለመንፈሳውያን አባቶች ለቄስ ለመነኵሴ ለአእሩግና ለሊቃውንት ለመምህራን ኹሉ ይነገራል፡፡ … (ሐተታ) አብ በጥሬነቱ ዘርፍ ይዞ ሲቀጸል ምስጢሩ ካባትነትና ከጌትነት ከባለቤትነት አይወጣም፡፡” [1] በማለት በግልጥ አስቀምጠውታል፡፡
     የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላትም፥ “ የወለደ፥ በሥርዓት ኮትኩቶ ያሳደገ፥ በሥጋና በመንፈስ የአባትነትን የፈጸ ሁሉ አባት ይባላል፡፡ … ምእመናን ከእርሱ በመንፈስ ቅዱስ ስለተወለዱ “አባ አባት” ብለው ይጠሩታል ፤ ማቴ.6፥9 ፤ ዮሐ.1፥12 ፡ 13 ፤ ገላ.4፥6” በሌላ ሥፍራም፥ “አብ ፤ አባት ማለት ነው፡፡ ይህ ስም ከዘለዓለም ከወልድና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ለነበረው ለእግዚአብሔር አብ የሕላዌ(የአንዋንዋር) ስሙ ነው(ማቴ.28፥19 ፤ 1ጴጥ.1፥1-2)፡፡ ኢየሱስ ስለሰማያዊ አባት ሲናገር ብዙ ጊዜ አብ ብሎ ጠራው፡፡” በማለት ቄስ ኮሊን ይገልጡታል፡፡ [2]

     በሌላ ትርጉምም “አባት ፤ (አብ) ወላጅ አስገኝ ፤ አሳዳጊ ፤ ሞግዚት ፤ መነኵሴ፡፡ (የነገር አባት) ፣ ጠበቃ ነገረ ፈጅ፡፡ (ያገር አባት) ፤ ሽማግሌ መካር ዛሬ አንዱ ቤት ነገ እሌላ ቤት እያደረ የሚጦር፡፡ … (የድኻ አባት) ድኻ ሰብሳቢ፡፡ (የንጀራ አባት) ፤ የናት ባል እንጀራ እያበላ ያሳደገ፡፡ … ” [3] በማለትም አስፍተው መተርጉማን ያስቀምጡታል፡፡
    ከእነዚህ የፍቺ መዝገበ ቃላት የምናስተውለው ትልቅ ቁም ነገር አባትነት ከጽንሰት እስከ ልደት ፤ ከልደት እስከእውቀት በሁለንተናው ከተወላጅ ልጅ ጋር ፍጹም ሥጋዊ ፣ ነፍሳዊ ፣ ዕውቀታዊ … ትስስርን የሚያሳይ ትልቅ ምስጢርን ያዘለ ትርጉም መሆኑን ነው፡፡ 

Thursday, 28 July 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና (ክፍል አንድ)

Please read in PDF
ያለነው እንደሸማኔ መወርወርያ በሚፈጥነውና በሚቸኩለው ዘመን ፤ ኃጢአትም ከተመሸገበትና ካደባበት ሥፍራው ላይ መገለጥና “እነሆ አለሁ” በሚለው አካላዊ ማንነቱን ማሳያ ዘመን ላይ ነን፡፡ ከቀደመው ዘመን ይልቅ የኃጢአት ጽዋ በዓለም መካከል ብቻ ሳይሆን “የእግዚአብሔር ነን” በሚሉትም መካከል እየሞላና እየፈሰሰ መሆኑን እያስተዋልን ነው፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ፦ “ … ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል” (2ጴጥ.3፥9) እንዲል እየሆነ ያለው እግዚአብሔር ስለሌለ አይደለም፡፡

Friday, 22 July 2016

ትልቅ ነው አምላኬ

Please read in PDF

ከፍ ከፍ በል ጉላና ድመቅ
ወገብህን አጽና ዝናርህን ታጠቅ
መስባትንም ስባ
ለድልደህም ወፍር
ሙሉ ብረት ለብሰህ ሸልልና ፎክር
በል በልብህ ጀምር ከ’ኔ ማን ሊወደር?

Thursday, 14 July 2016

“የ‘ፌስቡክ’ ትውልድ” (የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF
ምን እናድርግ?
1.     በእኒህ ማኅበራዊ የመረጃ መረቦች ላይ የሚጠቅመንንና መንፈሳዊ ነገሮቻችንን ብቻ ልናስተላልፍበት ፤ እንዲሁም የምናየውን ፣ የምናደምጠውን ፣ የምናነበውን ... ከእግዚአብሔር ቅዱስ ቃል ጋር የሚያቃርነን ነገር እንዳይሆን በብርቱ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የተጠራነው በቅድስና ሕይወት እንድንኖር ነው ፤ እርሱ የጠራን ቅዱስ ነውና(1ጴጥ.1፥14-16)፡፡
    “አባታችን ሆይ”፥ ብለን እግዚአብሔርን በጸሎት ከጠራን፥ እንደእግዚአብሔር ልጆች ለፈቃዱ ብቻ ልንታዘዝ ይገባል፡፡ እርሱ ፈቃዱ ቅድስና ነው፡፡ ቅድስና ከኃጢአት ከርኩሰት ተለይቶ ፤ ለእግዚአብሔር ብቻ መሆንን የሚፈልግ ዓቢይ ጉዳይ ነው፡፡ ሁላችን በየትኛውም ጉዟችን “ቅድስና ለእግዚአብሔር” የሚል አዲስ ኪዳን በክርስቶስ ኢየሱስ ገብተናል፥ ለዚህ ኪዳናችን ታማኞች በመሆን ሁሉን እንደቃሉ ልንመረምር ይገባናል፡፡