Wednesday, 30 December 2015

ሕይወት አልተስማማም!


ክፋትን በክፋት ፣ እያጠፉ መኖር
ርኩሰትን በርኩሰት ፣ እያጠፉ ማሴር

Thursday, 24 December 2015

ክርስቲያን ያልሆኑት ኦርቶክሳውያን ወይስ ምህረተ አብ?! (ክፍል አንድ)




     ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር” (2ጢሞ.3፥16) የእግዚአብሔር መንፈስ ያለባቸውን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትንም ሆነ የአዲስ ኪዳን መጻሕፍትን መንፈስ ቅዱስ ለእኛ የሰጠው፥ “ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ እናምን ዘንድ፥ አምነንም በስሙ ሕይወት ይሆንልን ዘንድ” ነው፡፡ (ዮሐ.20፥30-31)
      የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት አንድና አንድ ፤ ግልጽና ግልጽ እንጂ ስውርና ውስብስብ ፣ ለሰዎች እንዳይገባና እንዳይረዱት ተደርጎ የተጻፈ አይደለም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የሰው ልጅን የማዳን ተስፋና ተስፋው በኢየሱስ ክርስቶስ መምጣት ፤ መሞትና መነሳት የተፈጸመ መሆኑን በማስረዳት ይህን መዳን የምሥራች ብለን ለፍጥረት ሁሉ በድፍረት ከመንፈስ ቅዱስ ጉልበት የተነሳ እንድንናገር እንጂ ሌላ ስውር አጀንዳ የለውም፡፡ ጌታችን የመምጣቱን ምስጢር ራሱ ሲናገር፥ “እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ” (ዮሐ.10፥10) ሲል ፤ ደቀ መዛሙርቱም ፤ “ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው” (1ጢሞ.1፥15)  በማለት መሰከሩ፡፡ ለቤተ ክርስቲያንም የተሰጠው ትልቁ ተልእኮና አደራ “ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው” የሚል አለም አቀፍ ጥሪና ሰፊ የመከር ሥራ ነው፡፡ (ማቴ.28፥19)

Friday, 18 December 2015

ግጭትና ጦርነት የማያስተምራት አገር



ስለራሳችን እንዲህ እንናገራለን ፦
-      እንግዳ ተቀባይ ሕዝቦች ነን ፤
-      ብዙ ብሔር ብሔረሶችና ሕዝቦች ተዋደው የሚኖሩባት አገር አለን ፤
-      ለቁጥር የሚታክት “ክርስቲያን” ፣ እልፍ አዕላፍ ገዳም ፣ መድረክ የሚያጨናንቁ አገልጋይ ጳጳሳት ፣ ካህናት ፣ ዲያቆናትና ዘማርያን አሉን ፤
-      ከእኛ ወዲህ ማን አለ አማኝ? ከእኛ በላይ ጸዳቂ ፤ ታማኝ አገር ወዳድ ወዴት አለ?! …
ስንታይ ግን፦
-      “ባዕድ እንግዳ” ለመቀበል ሆዳችንን እንደአገር ስናሰፋ ፥ ከጎረቤትና ከወገናችን ጋር ግን “ጠብ ያለሽ በዳቦ” በሚል መንፈስ የተያዝን ፤
-      አገልጋዮቻችን ጸንሰው ወልደው ፣ አሳድገው የሰጡን አንዱ መልክ ዘረኝነትና ልዩነት ነው ፤
-      ከእኛ በላይ ሁሌም ሰው የለም ብንልም ዘወትር ግን እየኖርን ያለነው ከሰው በታች ጅራት ሆነን ነው …
     ሰሞኑን በከፊል የአገራችን ክፍል ብጥብጥና ሁከት ፤ ደም ማፍሰስና ግድያ ነግሶ ነበር፡፡ ይህን ሁሉ አድራጊው ሌላ ወራሪ ወይም እንግዳ አሸባሪ መጥቶብን አይደለም ፤ ሟችም እኛው፥ ገዳይም ያው እኛው ኢትዮጲያውያን ፤ ንብረት አውዳሚም፥ ንብረት የሚወድምበትም ያው የአንድ አገር ዜጎች ፤ የአንድ ርስት ወሰንተኞች ፤ የአንድ ወንዝ ጠጪዎች እኛው ነን፡፡
      እስኪ አስተውሉ፥ አንድ መቶ ዓመታት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በእኛና እኛ መካከል የተደረጉ ጦርነቶችን ብናነሳ፦ በ1909 ዓ.ም በራስ ተፈሪና በንጉሥ ሚካኤል መካከል በሰገሌ ፣ በ1922 ዓ.ም በራስ ተፈሪና በራስ ጕግሳ በአንቺም ወይም በበጌምድር ፣ ከ1966-1983 ዓ.ም ወታደራዊው መንግሥት ደርግና ኢሕአዴግ በተለያየ ቦታ ያደረጉት አስቀያሚ ጦርነት ፣ በ1994 ዓ.ም ሁለቱ “ወንድማማች” ኢትዮጲያና ኤርትራ ያደረጉትን ጦርነት (ወታደራዊው መንግሥት በአንድ ጉድጓድ የፈጃቸው የንጉሡ ዘመን መሪዎችና ሌሎችም ሳይካተቱ) ይህን ሁሉ ስናነሳ ምን ይታወሰናል?!

Tuesday, 15 December 2015

ቃሉ የሚለው፥ “ከቶ አላወቅኋችሁም ፤” ነው!

     

   በመጽሐፍ ቅዱስ በአገባቡ ወይም እንደተጻፈው ከማይነበቡ ጥቅሶች መካከል አንዱ፦ “ … ከቶ አላወቅኋችሁም ፤ እናንተ ዓመፀኞች ፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ።” (ማቴ.7፥23) በማለት የተጻፈልን ቃል ነው፡፡ ይህ ክፍልና ሌሎችም ከዚሁ ጋር የተያያዙም ንባባት ለአፈጻጸም ከፍ ያለ የሥነ ምግባርና የፍጽምናን መንገድ ይፈልጋሉ፡፡ ከዚህም የተነሳ ብዙዎች የተራራው ትምህርት ተብለው የሚታመኑትን ቃላት ማንም ሰው መፈጸም እንደማይቻለው ያስተምራሉ፡፡ በእርግጥም የእግዚአብሔርን ማናቸውንም ሥራ በእግዚአብሔር ጉልበት ፤ ራሱ እግዚአብሔርንም መማር የሚቻለን በራሱ በእግዚአብሔር ዕውቀት ገላጭነትና የጥበብ አስተማሪነት ነው፡፡ ይህ ማለት ግን የተራራውን ትምህርት በራሱ በእግዚአብሔር ጉልበትና መንፈስ መፈጸም ይቻለናል ማለት እንጂ ፈጽሞ መፈጸም አይቻልም ማለት አይደለም፡፡
     ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተራራው ትምህርቱ ያስተማራቸው ትምህርቶቹ በብዙዎች ዘንድ እጅግ የተደነቁና የሚያስደምሙ ትምህርቶች ናቸው፡፡ እውነትም! የእግዚአብሔር አምላካችን መንገድና ሕጉ ፤ ሥራውም ፍጹም ነውና (ዘዳግ.25፥15 ፤ መዝ.18፥30 ፤19፥7) ፤ እኛም በእርሱ ዘንድ (ዘዳግ.18፥13) ፤ እንደእርሱም ፍጹማን እንሆን ዘንድ ተጠርተናል፡፡ (ዘፍጥ.17፥1 ፤ ማቴ.5፥48 ፤ 19፥21) አዎን! የእግዚአብሔር ቅዱሳንም በፊቱ ያለነውርና ነቀፋ ነበሩ፡፡ (ዘፍጥ.6፥9 ፤ 1ነገ.11፥4 ፤ ኢዮ.1፥1 ፤ ሉቃ.1፥6 ፤ 2፥25) ፍጽምና ወይም በእግዚአብሔር ፊት የበቃ ሆኖ መገኘት ለሰው የሚቻል ነገር አይደለም (ሮሜ.3፥11 ፤ 2ቆሮ.3፥5) ስለዚህም ስለፍጽምናና ቅድስና ስናስብ በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል በተሰጠን ጸጋ እንጂ (ሮሜ.3፥21-24) በሕግ ወይም በራሳችን የምናደርገውም ፤ እናደርገውም ዘንድ የሚገባን አንዳችም ነገር የለም፡፡

Friday, 11 December 2015

ወንድሜ ማን ነው? (ክፍል ሁለት)

     

     ቃየን በልቡ ያሰላሰለውን ኃጢአት ከፍጻሜ ማድረስ አድብቷል፡፡ “ኃጢአተኞች እነሆ ቀስታቸውን ገትረዋልና፥ ፍላጻቸውንም በአውታር አዘጋጅተዋልና፥ ልበ ቅኖችን በስውር ይነድፉ ዘንድ።” (መዝ.10፥1) እንዲል ልበ ቅኑን አቤልን ይነድፍ ዘንድ ቃየን በስውር ይናደፍ ዘንድ ተነሳ፡፡ ስለዚህም፥ “ቃየንም ወንድሙን አቤልን፦ ና ወደሜዳ እንሂድ አለው።” ልምድ ያላቸው ወንጀለኞች “ትልቁ ክፋታቸው” ወንጀሉ እንዳይታወቅና ፤ እውነተኛ ፍርድ እንዳያገኙ የምስክር ደብዛ ያጠፋሉ፡፡
       ቃየን ወንድሙን “ወደሜዳ እንሂድ” ያለው አብሮት ሊጫወት ፤ እንደወንድምም ሊያወጋው አይደለም፡፡  አቤል ግን ወንድሜ እንዲህ ያደርግብኛል ስላላለ አብሮት ሄደ፡፡ ለዳኝነት ብይን መስጫው ቁልፉ ምስክር ወይም ማስረጃ ነው፡፡ ቃየን ያለምስክር “በሜዳም ሳሉ ቃየን በወንድሙ በአቤል ላይ ተነሣበት፥ ገደለውም።” (ዘፍጥ.4፥8) የጨለማ ሥራ ካልተሸሸገ በቀር ብቻውን መቆም አይችልም፡፡ “የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ።” (ዮሐ.8፥44) እንደተባለ የዲያብሎስን ፈቃድ ሊያደርግ እግሩን አስቸኰለ፡፡ ኃጢአተኞች ትልቁን ምስክር ህሊናቸውን ዘንግተው የሰው ምስክር ይሸሻሉ፡፡ እግዚአብሔር ግን ሁሉን ያያል!!!

Sunday, 6 December 2015

ጌታ ካላለበት



ከመድረኩ ቆመህ ከአውደ ምህረቱ፤
ተፋተህ ተራቁተህ ከእግዚአብሔር ፍርሃቱ፤
“በʻኔ የሚናገር ጌታ ነው” በማለት፤
ለምን ትጮኻለህ? የውስጥህን ክህደት፤

Friday, 4 December 2015

ድንግል ማርያም በድንግል ማርያም አንደበት (የመጨረሻ ክፍል)


6.  የእግዚአብሔርን መጋቢነት

           “የተራቡትን በበጎ ነገር አጥግቦአል ፤ ባለ ጠጎችንም ባዶአቸውን ሰዶአቸዋል።” (ሉቃ.1፥53)

      እግዚአብሔር የተራቡትን ከመራባቸው በፊት አዝኖ ሲያስብላቸው (ዘፍጥ.41፥25 ፤ ሐዋ.11፥28) ፤ በተራቡና በሚያስፈልጋቸው ጊዜ ሲያጠግባቸው አይተናል፡፡ (ዘፍጥ.41፥54-56 ፤ ዘጸ.16፥6-18 ፤ ማቴ.6፥26 ፤ 31-32) ድንግል ማርያም በምድር ላይ ትኖር በነበረችበት ወራት ድኃ እንደነበረች የሚያሳየን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል አለ፡፡ (ሉቃ.2፥22-24) በእርሱ መጥገብንም በሚገባ ታውቀዋለች፡፡ እንዲህ ያለውን ምስክርነት “ጠግበው የነበሩ እንጀራ አጡ፥ ተርበው የነበሩ ከራብ ዐርፈዋል” በማለት ቅድስት ሐናም ምስክርነት ስትሰጥ እናያለን፡፡ (1ሳሙ.2፥6)

Tuesday, 1 December 2015

የኖድ ምድሩ ሰው (ዘፍጥ.4፥16)

     

    እግዚአብሔር ፍጥረትን ከፈጠረበት ጥበብ በሚልቅ ጥበብ፥ የሰውን ልጅ ፈጠረው፡፡ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት እንደሚሉትም ሌሎቹን በቃልና በዝምታ ሲፈጥር ሰውን ግን “በእጁ አበጅቶ ግብር እምግብር” ፈጠረው ይሉናል፡፡ በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችም፥ ሰው እጅግ በታላቅ ክብርና ሞገስ መፈጠሩን ይናገራሉ፡፡ (ዘፍ.1፥27 ፤ 2፥7 ፤ መዝ.139፥14 ፤ 145፥10) ዕለትም ዕለትም ከእግዚአብሔር ጋር እጅግ የሚያስደንቅ ንግግርና ጨዋታ ያደርግ እንደነበርም ታላቁ መጽሐፍ ሲነግረን ልባችን እጅግ መደመሙና እጁን በአፍ ጭኖ መደነቁ አይቀርም ፤ ትልቁ ጌታ ከፍጡሩ ጋር ዕለት ዕለት እንደመነጋገር የሚያስደንቅ ምን አለ!? (ዘፍጥ.3፥8)
     ታላቁ መጽሐፍ፥ ዘፍጥረት ምዕራፍ አንድንና ሁለትን እጅግ የሚደንቅ ትስስር ከአምላኩ ጋር እንደነበረው የሚነግረን ብዙም ሳይርቅ በሦስተኛው ምዕራፍ አሳዛኙን ውድቀት ይነግረናል፡፡ ዔደን ገነት ልዩና የእግዚአብሔር ሠላም የሰፈነባት ሆና ለሰው ልጅ የተሰጠች ፤ እንዲሁም የሰው ልጅ ቅዱስና ጻድቅ እግዚአብሔር ራሱን በሚገልጥበት በኪሩቤል አጠገብ መኖር እንዳልሆነለት ፥ በኃጢአት ምክንያት ሁከት ፣ ፍርሃት ፣ ሽሽት ፣ ዔደን ገነት ጭንቀት የሰፈነባት ሆና ሰው ማረፊያ ሲያጣባት እናስተውላለን፡፡  ኖድ ማለት የስሙ ትርጓሜ መቅበዝበዝ ማለት ነው፡፡

Friday, 27 November 2015

ወንድሜ ማን ነው? (ክፍል አንድ)

    
        Please read in PDF

  ይህን ጽሁፍ ከመጻፌ በፊት ለብዙ ሰዓታት ውስጤ ከገለባ ይልቅ እስኪቀልብኝ ድረስ “አስቀድሞ ነገር፥ እኔ ራሴ ለሌላው በተለይም ለሃይማኖት ቤተ ሰዎቼ ወንድም መሆን እችላለሁኝ?” ብዬ ከራሴ ጋር ተሟግቻለሁኝ፡፡ ምናልባት ጥያቄው ያን ያህል ከባድ ላይመስል ይችላል ፤ ይህን ጥያቄ ይዘን ወደታላቁ መጽሐፍ ሚዛንነት የተጠጋንና ራሳችንንም በታላቁ መጽሐፍ ሚዛንነት ያየን እንደሆን ግን እጅግ የሚስቡና እይታችንን የሚያጠሩ እውነቶችን እናስተውላለን፡፡
      “ወንድም” የሚለውን ቃል ታላቁ መጽሐፍ ሲፈታው፥ ከአንድ እናትና አባት የሚወለዱትን ብቻ ሳይሆን የአንድ አገር ተወላጆችን (ዘጸ.2፥11 ፤ ሐዋ.7፥23-26) ፤ ከጥብቅ ወዳጅነት የተነሳ እጅግ የተቀራረቡትን (2ሳሙ.1፥26-27) ፤ ከቅርብ ዘመድ የተነሳ የተወዳጁትን (ዘፍ.36፥10 ፤ ዘኊል.20፥14 ፤ ሮሜ.9፥3) ፤ በቃል ኪዳንም (1ነገ.5፥1 ፤ 12) ወንድማማችነት እንዳለ ይነግረናል፡፡ ወንድማማችነት ምንም እንኳ መሠረቱ በደም መወለድ ቢሆንም፥ ከዚሁ ጋር ሊተካከል በሚችል መልኩ ደግሞ ታላቁ መጽሐፍ በአላማ የተሳሰሩትን እኩል አስተካክሎ ያስቀምጣል፡፡

Monday, 23 November 2015

ግድ የለም ታገሰው



ጌታ …
ዝም ያለ ሲመስል
በጆሮ እንዳልሠማ
በአይኑም እንዳላየ
                        ቀና ቀና ይላል
                        የመከራው መከር
                        ጭንቅ እያበራየ

Monday, 16 November 2015

ድንግል ማርያም በድንግል ማርያም አንደበት (ክፍል ስድስት)




5.  እግዚአብሔርፍርድያደላድላል

“ … ትዕቢተኞችን በልባቸው አሳብ በትኖአል ፤ ገዥዎችን ከዙፋናቸው አዋርዶአል ፤ ትሑታንንም ከፍ አድርጎአል” (ሉቃ.1፥51-52)

    ብዙዎቻችን የክፉዎችን ክፋት አይተን፥ ለእግዚአብሔር ከማሳሰብና በፊቱ ጥቂት ከመታገስ ካለመቻልም በላይ፥ በብዙ ማጉረምረም የተጠመድን ነን ፤ በውጪው አለም የሚኖሩ እልፍ አዕላፍ ዲያስፖራዎቻችንና አገር ቤትም ያሉ ጥቂት የማይባሉ ወገኖች መንግሥት በመክሰስ የተጠመዱ ናቸው፡፡ አንድ ነገር እንደአማኝ እጅግ አምናለሁ ፥ መንግሥት ያጥፋም ፤ አያጥፋም ከሁሉ በፊት ጸሎት እንደሚገባው (1ጢሞ.2፥1-2) ፤ የሚያጠፋ ከሆነም ደግሞ በአገባቡ ሊመከር ፣ ሊወቀስ  ፣ ሊገሰጽ እንዲገባው አምናለሁ፡፡ ይህን ሳያደርጉ ከመሬት ተነስቶ ቱግ ማለት ከድንግል ማርያም የምስጋና ቃል አለመማር ነው፡፡ 

Tuesday, 10 November 2015

ከፍቶታል በሩን






የሴቲቱ ዘር፥ የእባቡን ራስ ʼሚቀጠቅጠቀው፤
የአብርሃም ዘር፥ የምድርን ነገድ የሚባርከው፤
ከዳዊት ወገብ፥ በትር የሚሆነው ለምለም ቁጥቋጦ፤

Wednesday, 4 November 2015

ጣሊያናዊው የደብር አለቃና - የተከሰሰበት ግብረ ሰዶማዊነቱ




 Please read in PDF

       ስለተከሰሱ ሰዎች መብት የኢትዮጲያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ መንግሥት ሕገ መንግሥት “በፍርድ ሂደት ባሉበት ጊዜ በተከሰሱበት ወንጀል እንደጥፋተኛ ያለመቆጠር ፥ መብት አላቸው፡፡” በማለት ይገልጣል፡፡ (ሕ/መን.አን.20(3)) ነገር ግን “ሕጻናትን የሚመለከቱ እርምጃዎች በሚወሰዱበት ጊዜ በመንግሥታዊ ፥ ወይም በግል የበጎ አድራጎት ተቋሞች ባለ ሥልጣኖች ወይም በሕግ አውጪ አካላት፥ የሕጻናት ደህንነት በቀደምትነት መታሰብ አለበት፡፡”
    በቀደምትነት መታሰብ ያለበት ብቻ ሳይሆን ፦
“ማንኛውም ሕጻን ጉልበቱን ከሚበዘብዙ ልማዶች የመጠበቅ ፥ በትምህርቱ፥ በጤናውና በደህንነቱ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ሥራዎች እንዲሠራ ያለመገደድ ወይም ከመሥራት የመጠበቅ መብትም እንዳለው” በግልጥ አስቀምጧል፡፡
(ሕገ መን.አን.36(1)መ)

Wednesday, 28 October 2015

ኢየሱስን የሚጋርዱ - ባህላዊ “ሰባኪ” ዎቻችን



       
                                                 Please read in PDF

     የክርስቶስ አገልጋይ ትጥቁ አጭር (ማቴ.10፥5-11) ፤ ዕለት ዕለት መስቀሉን ተሸክሞ በመከተል የሚኖር (ማር.8፥34) ፤በቁም ሳለ ከሚገድል ቅምጥልነት የራቀና “ወደዓለም ምንም እንኳ አላመጣንምና፥ አንዳችንም ልንወስድ አይቻለንም፤ ምግብና ልብስ ከኖረን ግን፥ እርሱ ይበቃናል።” የሚል ቅዱስ አቋም ያለው (1ጢሞ.5፥6 ፤ 6፥7-8) ፤ በሕይወቱ (ሮሜ.12፥2) ፣ በንግግሩ (ቈላ.4፥6) ፣ በመንገዱ ሁሉ የአምላኩን ስም የሚያስመሠግንና ከማስነቀፍ ፈጽሞ የራቀ ፤ ለሁልጊዜ ለፈጣሪው የሚያደላና የሚኖር ፤ ለሕይወቱ ምሳሌና መርሕ የሚሆነውን ነገር ለመፈለግ ሁልጊዜ እግረ ልቡን ወደ ታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ የሚያቀና ሊሆን ይገባዋል፡፡ (ሐዋ.17፥10 ፤ 1ዮሐ.4፥1)
እንዲህ ስል አገልጋይ ባዕለ ጠጋ መሆን የለበትም የሚል አቋም የለኝም ፤ ዳሩ ግን አማኝም ሆነ አገልጋይ መሠረታዊ የሆነውን ነገር፥ ማለትም ምግብን ፣ ልብስንና መጠለያ በማግኘቱ ፣ እርካታ ይኖረው ዘንድ አስፈላጊ ፤ የተገባም ነው፡፡ ይህ ማለት አገልጋይ እንደሚሠራው ሁሉ አገባብ ያለው ደመወዙ ይገባዋል ማለት ነው፡፡ እንዲሁ ገንዘብ የሚጠይቅ የተለየ ነገ ርቢከሰት ፣ በልግስና በመስጠት እግዚአብሔርን እያገለገለ (2ቆሮ.8፥3 ፤ 9፥6) “በመከራ ቀን ጥራኝ፥ አድንህማለሁ አንተም ታከብረኛለህ።” እንዲል፥ እግዚአብሔር እንዲሰጠው ወደእርሱ መመልከት ይኖርበታል፡፡ (መዝ.50፣15) ይህንን የምንለው ሁልጊዜ መንግሥቱንና ጽድቁን መቅደምና ማስከተል ከሌለብን ብቻ ነው፡፡ (ማቴ.6፥33)

Friday, 23 October 2015

የፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ንግግር ሳጤነው ምጥ አለበት!!!


ብዙዎች ያልጨከንለትና ያልደፈርንለት እውነት!!!

      በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በተካሄደው 34  መደበኛ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ፥ ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ጥቅምት 8 ቀን  2008 ዓ.ም ካስተላለፉት አባታዊ መልዕክት የሚከተለው መልዕክት ላይ ማተኮር ፈለግሁ፡፡
 
“ … የምዕመናን ፍልሰት በየጊዜው እየጨመረ የመሄዱ መነሻ ምስጢር ምንድን ነው? የሚለውን ጥያቄ ቤተ ክርስቲያናችን በአጽንዖት ልታጤነው ይገባል ፤ በዚህ ዙርያ የሚታየው ክፍተት ፈጣን ምላሽ በመስጠት መግቻ ካላበጀንለት ነገ ከባድ የሃይማኖትና የታሪክ ወቀሳ ማስከተሉ እንደማይቀር ልብ እንበል፡፡
     ለመሆኑ ምዕመናን ከቤተ ክርስቲያናችን እየወጡ  ወደሌላ ካምብ ለመግባት ለምን መረጡ?
-       የሚያስተምራቸውን ካህን አጥተው ነውን?
-       የቤተ ክርስቲያናችን ትምህርተ ሃይማኖት ክፍተት ኖሮት ነው?
-       የቤተ ክርስቲያችን አስተዳደር የማያረካ ሆኖ ነውን?
-       የካህን እጥረት ስላለ ነውን?
-       ወይስ ሌሎች ከእኛ የተሻሉ ሆነው ስለተገኙ ነው፤?
የዚህ ሁሉ መልስ በእያንዳንዳችን ኅሊና ውስጥ ቁልጭ ብሎ ስለሚታወቅ የጥያቄው መልስ ለእናንተው ሰጥተናል፡፡  … ”

     ደግሞም ልቀጥል፦ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መጀመርን አስመልክቶ ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም  ቅዱስነታቸው በሰጡትም መግለጫም እንዲህ አሉ፦