Please Read in PDF
በህይወት የማይስማሙ በሞት ይጣመራሉ፡፡በክርስቶስ የሚካካዱ ለሰይጣን ሊገዙ በአንድ ያብራሉ፡፡በምድረ በዳ ሰው ለመግደል ፣የሰው ንብረት ለመዝረፍ የሚስማሙ ቀራንዮ ላይ መለያየት ይጀምራሉ፡፡በወንበዴነት የሚስማሙ የክርስቶስ በመባል ግን ይለያያሉ፡፡በኃጢአት የሚጣበቁ በጽድቅ ይነጣጠላሉ፡፡አይለያዩም የተባሉ የኃጢአት ባልንጀሮች ክርስቶስን በማመንና ባለማመን እስከማይተዋወቁ ድረስ ይከፋፋሉ፡፡
በህይወት የማይስማሙ በሞት ይጣመራሉ፡፡በክርስቶስ የሚካካዱ ለሰይጣን ሊገዙ በአንድ ያብራሉ፡፡በምድረ በዳ ሰው ለመግደል ፣የሰው ንብረት ለመዝረፍ የሚስማሙ ቀራንዮ ላይ መለያየት ይጀምራሉ፡፡በወንበዴነት የሚስማሙ የክርስቶስ በመባል ግን ይለያያሉ፡፡በኃጢአት የሚጣበቁ በጽድቅ ይነጣጠላሉ፡፡አይለያዩም የተባሉ የኃጢአት ባልንጀሮች ክርስቶስን በማመንና ባለማመን እስከማይተዋወቁ ድረስ ይከፋፋሉ፡፡
ቀራንዮ ድካማችን አይጸድቅባትም፡፡ድካማችንን በመስቀሉ ጠርቀን፤
ክፉ ምኞት አንቂ አሮጌውን ሰው ሰቅለን አዲሱን ሰው የምንለብስባት፤ ለአንዱ ጌታ መገዛታችንን በግልጥ ውሳኔያችንን
የምንገልጥባት ስፍራ ናት፡፡ቀራንዮ ላይ ብዙ አማራጮች ብዙ መንገዶች የሉም፡፡ብዙ የመዳን ቀመሮች ፣ከሁለት የዘለሉ የድህነት
ስሌቶችም የሉም፡፡ቀራንዮ ላይ ሁለት መንገዶች ብቻ አሉ፡፡አንዱ የሲዖል አንዱ ወደእግዚአብሔር ገነት፡፡ሦስተኛ ምርጫ
የለም፡፡ብንፈልግም ፈጽሞ ማግኘት አይሆንልንም፡፡
አንደኛው መስቀል ላይ ዘመኑን በውንብድና የጨረሰ፣ለክፋቱ ዳርቻ
ሳያበጅ ከነክፋቱ የተገኘ ለጥፋቱም ተካካይ ፍርድ በህጉ የተሰጠው አንድ ደካማ ሰው አለ፡፡አለም ሞት ብትፈርድበትም ክርስቶስ
ግን ዛሬም የርህራሔ እጁን ዘርግቶ እስከማታ "ልጄ ሆይ አትሙትብኝ እኔ ልሙትልህ!!!" እያለ ይለምነዋል፡፡ ከእግዚአብሔር
መዝገብ ፍርድ እስካልወጣ አለም ሞት ፈርዳ ለፍርዱ መፈጸም ብትቻኮልም የህይወት ጥላችንን ማንም አያጥፈውም፡፡አለም ሞት
ብትደግስም ክርስቶስ ግን የማይደክም የማዳን እጅ ዘርግቶለታል፡፡

